ዘዳግም 33:6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ሮቤልን እፈልገዋለሁ፤ አይሙትብኝ፤ ቍጥሩም ብዙ ይሁን። አዲሱ መደበኛ ትርጒም “ሮቤል በሕይወት ይኑር፤ አይሙት፤ የወገኖቹ ቍጥርም አይጕደልበት።” መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) “ሮቤል በሕይወት ይኑር፥ አይሙት፥ ሰዎቹም በቍጥር አይነሱ።” አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሙሴ ሰለ ሮቤል ነገድ እንዲህ አለ፦ “ምንም እንኳ ብዛቱ ጥቂት ቢሆን፥ ጌታ ሆይ የሮቤል ነገድ ይኑር እንጂ አይሙት።” መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ሮቤል በህይወት ይኑር፥ አይሙት፤ 2 ሰዎቹም በቁጥር ብዙ ይሁኑ፤ |
“ይሁዳ፥ ወንድሞችህ አንተን ያመሰግኑሃል፤ እጅህ በጠላቶችህ ደንደስ ላይ ነው፤ የአባትህ ልጆች በፊትህ ይሰግዳሉ።