La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘዳግም 14:8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

እር​ያም፥ ሰኰ​ናው ስለ​ተ​ሰ​ነ​ጠቀ፥ ጥፍ​ሩም ከሁ​ለት ስለ​ተ​ከ​ፈለ፥ ነገር ግን ሰለ​ማ​ያ​መ​ሰኳ፥ እርሱ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው፤ ሥጋ​ዉን አት​ብሉ፤ በድ​ኑ​ንም አት​ንኩ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ዐሣማም እንደዚሁ ርኩስ ነው፤ ምንም እንኳ ሰኰናው የተሰነጠቀ ቢሆንም፣ ስለማያመሰኳ፣ እርሱ ለእናንተ ንጹሕ አይደለም፤ የእነዚህን ሥጋ አትብሉ፤ ጥንባቸውንም አትንኩ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ዐሣማም፥ ምንም እንኳ ሰኰናው የተሰነጠቀ ቢሆንም ስለማያመሰኩህ፥ እርሱ ለእናንተ ንጹሕ አይደለም፤ የእነዚህን ሥጋ አትብሉ፤ ጥምባቸውንም አትንኩ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ዐሣማዎችን አትብሉ፤ እነርሱ ሰኮናቸው የተከፈለ ቢሆንም ስለማያመሰኩ የረከሱ ሆነው ይቈጠራሉ፤ እንደነዚህ ያሉትን እንስሶች መብላት ይቅርና በድናቸውን እንኳ አትንኩ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

እርያም ሰኮናው ስለ ተሰነጠቀ ነገር ግን ስላላመሰኳ፥ እርሱ ለእናንተ ርኩስ ነው፤ ሥጋውን አትብሉ፥ በድኑንም አትንኩ።

Ver Capítulo



ዘዳግም 14:8
10 Referencias Cruzadas  

በመ​ቃ​ብ​ርም መካ​ከል የሚ​ተኙ፥ በዋሻ ውስጥ የሚ​ያ​ልሙ፥ የእ​ሪያ ሥጋም የሚ​በሉ ናቸው። የመ​ሥ​ዋ​ዕ​ታ​ቸ​ውን ደምና ዕቃ​ቸ​ው​ንም ሁሉ ያረ​ክ​ሳሉ።


“በአ​ት​ክ​ልት ቦታ ውስጥ ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን የሚ​ያ​ጠ​ሩና የሚ​ያ​ነጹ፥ በም​ግብ ቦታም የእ​ሪ​ያን ሥጋ፥ አስ​ጸ​ያፊ ነገ​ር​ንም አይ​ጥ​ንም የሚ​በሉ በአ​ን​ድ​ነት ይጠ​ፋሉ፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


በሬን የሚ​ሠ​ዋ​ልኝ ኃጥእ ውሻን እን​ደ​ሚ​ያ​ር​ድ​ልኝ ነው፤ የእ​ህ​ልን ቍር​ባን የሚ​ያ​ቀ​ር​ብም የእ​ሪ​ያን ደም እን​ደ​ሚ​ያ​ቀ​ርብ ነው፤ ዕጣ​ን​ንም ለመ​ታ​ሰ​ቢያ የሚ​ያ​ጥን አም​ላ​ክን እን​ደ​ሚ​ፀ​ርፍ ነው፤ እነ​ዚህ የገዛ መን​ገ​ዳ​ቸ​ውን መረጡ፤ ነፍ​ሳ​ቸ​ውም በር​ኵ​ሰ​ታ​ቸው ደስ ይላ​ታል።


የተ​ሰ​ነ​ጠቀ ሰኰና ያለ​ው​ንና የሚ​ያ​መ​ሰ​ኳ​ውን እን​ስሳ ሁሉ ብሉ።


ርኩስ ነገ​ርን፥ የሞ​ተ​ውን፥ አውሬ የነ​ከ​ሰ​ውን፥ ወይም የበ​ከተ፥ ወይም የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀስ የእ​ን​ስ​ሳን በድን የነካ፥ ከእ​ር​ሱም ያነሣ ሰው ቢኖር፤


ነገር ግን ከሚ​ያ​መ​ሰኩ ወይም ሰኰ​ና​ቸው ከተ​ሰ​ነ​ጠቀ እነ​ዚ​ህን አት​በ​ሉም፤ ግመ​ልን፥ ሽኮ​ኮን፥ ጥን​ቸ​ልን አት​በ​ሉም፤ ያመ​ሰ​ኳ​ሉና፥ ነገር ግን ሰኰ​ና​ቸው አል​ተ​ሰ​ነ​ጠ​ቀ​ምና እነ​ዚህ ለእ​ና​ንተ ርኩ​ሳን ናቸው።


“በው​ኆች ውስጥ ከሚ​ኖ​ሩት ሁሉ የም​ት​በ​ሉ​አ​ቸው እነ​ዚህ ናቸው፤ ክን​ፍና ቅር​ፊ​ትም ያላ​ቸ​ውን ትበ​ላ​ላ​ችሁ፤


“ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፤” ደግሞ “የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች፤” እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል።