Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ዘዳግም 14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የተ​ከ​ለ​ከለ የል​ቅሶ ልማድ

1 “ለሞተ ሰውም በዐ​ይ​ና​ችሁ መካ​ከል ፊታ​ች​ሁን አት​ንጩ፤ ራሳ​ች​ሁ​ንም አት​ላጩ፤

2 ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አንተ ቅዱስ ሕዝብ ነህና፥ በም​ድ​ርም ላይ ከሚ​ኖሩ አሕ​ዛብ ሁሉ ይልቅ ለእ​ርሱ ለራሱ ሕዝብ ትሆ​ን​ለት ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አን​ተን መር​ጦ​አ​ልና።


የሚ​በ​ሉና የማ​ይ​በሉ እን​ስ​ሶች
( ዘሌ. 11፥1-47 )

3 “ርኩ​ስን ነገር ሁሉ አት​ብሉ።

4 የም​ት​በ​ሉ​አ​ቸው እን​ስ​ሶች እነ​ዚህ ናቸው፤ በሬ፥ በግ፥ ፍየል፥

5 ዋልያ፥ ሚዳቋ፥ የበ​ረሃ ፍየል፥ ጎሽ፥ ብሖር፥ ሳላ፥ ድኵላ።

6 ከእ​ን​ስ​ሶች ሰኰ​ናው የተ​ሰ​ነ​ጠ​ቀ​ውን፥ ጥፍ​ሩም ከሁ​ለት የተ​ከ​ፈ​ለ​ውን፥ የሚ​ያ​መ​ሰ​ኳ​ው​ንም እን​ስሳ ሁሉ ትበ​ላ​ለህ።

7 ነገር ግን ከሚ​ያ​መ​ሰኩ ወይም ሰኰ​ና​ቸው ከተ​ሰ​ነ​ጠቀ እነ​ዚ​ህን አት​በ​ሉም፤ ግመ​ልን፥ ሽኮ​ኮን፥ ጥን​ቸ​ልን አት​በ​ሉም፤ ያመ​ሰ​ኳ​ሉና፥ ነገር ግን ሰኰ​ና​ቸው አል​ተ​ሰ​ነ​ጠ​ቀ​ምና እነ​ዚህ ለእ​ና​ንተ ርኩ​ሳን ናቸው።

8 እር​ያም፥ ሰኰ​ናው ስለ​ተ​ሰ​ነ​ጠቀ፥ ጥፍ​ሩም ከሁ​ለት ስለ​ተ​ከ​ፈለ፥ ነገር ግን ሰለ​ማ​ያ​መ​ሰኳ፥ እርሱ ለእ​ና​ንተ ርኩስ ነው፤ ሥጋ​ዉን አት​ብሉ፤ በድ​ኑ​ንም አት​ንኩ።

9 “በው​ኆች ውስጥ ከሚ​ኖ​ሩት ሁሉ የም​ት​በ​ሉ​አ​ቸው እነ​ዚህ ናቸው፤ ክን​ፍና ቅር​ፊ​ትም ያላ​ቸ​ውን ትበ​ላ​ላ​ችሁ፤

10 ክን​ፍና ቅር​ፊ​ትም የሌ​ላ​ቸ​ውን አት​በ​ሉም፤ ለእ​ና​ንተ ርኩ​ሳን ናቸው።

11 “ንጹ​ሓን የሆ​ኑ​ትን ወፎች ሁሉ ብሉ።

12 ሊበሉ የማ​ይ​ገ​ባ​ቸው ግን እነ​ዚህ ናቸው፤ ንስር፥ ገዴ፥ ዓሣ አውጭ።

13 ጭል​ፊት፥ ጭላ​ትና መሰ​ሎ​ቻ​ቸው፥

14 ቍራና መሰ​ሎቹ፤

15 ሰጎን፥ አራት ራስ አሞራ፥ ዝዪ፥ በቋል በየ​ወ​ገኑ።

16 ጉጉት፥ ጋጋኖ፥ የውኃ ዶሮ።

17 ይብራ፥ ጥምብ አንሣ አሞ​ራና መሰ​ሎ​ቻ​ቸው፥

18 ዕር​ኩም፥ ሽመላ፥ ሳቢ​ሳና መሰ​ሎቹ፥ ጅን​ጅ​ላቴ ወፍ፥ የሌ​ሊት ወፍ።

19 የሚ​በ​ር​ሩም አዕ​ዋፍ ሁሉ ለእ​ና​ንተ ንጹ​ሓን አይ​ደ​ሉ​ምና ከእ​ነ​ርሱ አት​ብሉ፤

20 ነገር ግን ንጹ​ሓን የሆ​ኑ​ትን ወፎች ሁሉ ብሉ።

21 የበ​ከ​ተ​ዉን ሁሉ አት​ብሉ፤ ይበ​ላው ዘንድ በሀ​ገ​ርህ ደጅ ለተ​ቀ​መጠ መጻ​ተኛ ወይም ለባ​ዕድ ስጠው፤ አንተ ለአ​ም​ላ​ካህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ቀ​ደሰ ሕዝብ ነህና፥ የፍ​የ​ሉን ጠቦት በእ​ናቱ ወተት አት​ቀ​ቅል።


የዐ​ሥ​ራት አወ​ጣጥ ሕግ

22 “ከእ​ር​ሻህ ዘር​ተህ በየ​ዓ​መቱ ከም​ታ​ገ​ኘው እህ​ልህ ሁሉ ዐሥ​ራት ታወ​ጣ​ለህ።

23 በዘ​መ​ን​ህም ሁሉ አም​ላ​ክ​ህን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራ​ትን ትማር ዘንድ፥ ስሙ እን​ዲ​ጠ​ራ​በት በመ​ረ​ጠው ስፍራ በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት የእ​ህ​ል​ህን፥ የወ​ይ​ን​ህን፥ የዘ​ይ​ት​ህ​ንም ዐሥ​ራት፥ የላ​ም​ህ​ንና የበ​ግ​ህ​ንም በኵ​ራት ብላ።

24 አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባር​ኮ​ሃ​ልና፥ መን​ገዱ ሩቅ ቢሆን፥ አም​ላ​ክ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስሙን ያኖ​ር​በት ዘንድ የመ​ረ​ጠው ስፍራ ቢር​ቅ​ብህ፥ ይህን ወደ​ዚያ ለመ​ሸ​ከም ባት​ችል፥

25 በብር ትሸ​ጠ​ዋ​ለህ፤ ብሩ​ንም በእ​ጅህ ይዘህ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወደ መረ​ጠው ስፍራ ትሄ​ዳ​ለህ።

26 በዚ​ያም በብሩ ሰው​ነ​ትህ የፈ​ለ​ገ​ውን፥ በሬ ወይም በግ፥ ወይም የወ​ይን ጠጅ፥ ወይም ብርቱ መጠጥ፥ ሰው​ነ​ትህ የሚ​ሻ​ውን ሁሉ ትገ​ዛ​ለህ፤ በዚ​ያም በአ​ም​ላ​ክህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ትበ​ላ​ዋ​ለህ፤ አን​ተና ቤተ ሰብ​ህም ደስ ይላ​ች​ኋል።

27 ድር​ሻና ርስት ከአ​ንተ ጋር ስለ​ሌ​ለው በከ​ተ​ማህ ውስጥ ያለ​ውን ሌዋዊ ቸል አት​በል።

28 “በየ​ሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት መጨ​ረሻ በዚያ ዓመት የፍ​ሬ​ህን ዐሥ​ራት ሁሉ አም​ጥ​ተህ በከ​ተ​ማ​ዎ​ችህ ውስጥ ታኖ​ረ​ዋ​ለህ።

29 ሌዋ​ዊ​ዉም፥ ከአ​ንተ ጋር ክፍ​ልና ርስት የለ​ው​ምና፥ በከ​ተ​ማህ ውስጥ ያለ መጻ​ተኛ፥ ድሃ-አደ​ግም፥ መበ​ለ​ትም መጥ​ተው ይበ​ላሉ፤ ይጠ​ግ​ባ​ሉም፤ ይኸ​ውም አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በም​ታ​ደ​ር​ገው በእ​ጅህ ሥራ ሁሉ ይባ​ር​ክህ ዘንድ ነው።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos