ከዚህም በኋላ ይህን ነገር በሰማ ጊዜ አብረውት ካሉት ከነገሥታቱ ሁሉ ጋር በድንኳኑ ውስጥ ይጠጣ ነበር፤ አገልጋዮቹንም፥ “ከተማውን እጠሩት” አላቸው። እነርሱም በከተማዪቱ ትይዩ ተሰለፉ።
2 ነገሥት 10:20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ኢዩም፥ “ለበዓል መሥዋዕታችሁን አንጹ” አላቸው፤ እነርሱም አዋጅ ነገሩ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ኢዩም፣ “ለበኣል ክብር ጉባኤ ጥሩ” አለ፤ እነርሱም ይህንኑ ለሕዝቡ አስታወቁ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ከዚህም በኋላ ኢዩ “በዓል ተብሎ ለሚጠራው ጣዖት ክብረ በዓል ይደረግ!” ሲል ትእዛዝ ሰጠ፤ ይህም በዐዋጅ ተነገረ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከዚህም በኋላ ኢዩ “ባዓል ተብሎ ለሚጠራው ጣዖት ክብረ በዓል ይደረግ!” ሲል ትእዛዝ ሰጠ፤ ይህም በዐዋጅ ተነገረ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ኢዩም “ለበኣል ዋና ጉባኤ ቀድሱ፤” አለ። እነርሱም አወጁ። |
ከዚህም በኋላ ይህን ነገር በሰማ ጊዜ አብረውት ካሉት ከነገሥታቱ ሁሉ ጋር በድንኳኑ ውስጥ ይጠጣ ነበር፤ አገልጋዮቹንም፥ “ከተማውን እጠሩት” አላቸው። እነርሱም በከተማዪቱ ትይዩ ተሰለፉ።
ከእጃቸውም ተቀብሎ በመቅረጫ ቀረጸው፤ ቀልጦ የተሠራ ጥጃም አደረገው፤ እርሱም፥ “እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር ያወጡህ አማልክትህ ናቸው” አላቸው።
ጾምን ቀድሱ፤ ምህላንም ዐውጁ፤ ሽማግሌዎቹንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም በአንድነት ጩኹ።