La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




1 ነገሥት 4:30 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የሰ​ሎ​ሞ​ንም ጥበብ ከቀ​ደሙ ሰዎች ሁሉ ጥበ​ብና ከግ​ብፅ ጥበብ ሁሉ በዛ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

የሰሎሞን ጥበብ ከምሥራቅ ሰዎች ሁሉ ጥበብ በጣም የላቀ ከግብጽም ጥበብ ሁሉ የበለጠ ነበር፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ሰሎሞን ከምሥራቅ አገርና ከግብጽም ጥበበኞች እጅግ የላቀ ጥበብ ነበረው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ሰሎሞን ከምሥራቅ አገርና ከግብጽም ጥበበኞች እጅግ የላቀ ጥበብ ነበረው፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

የሰሎሞንም ጥበብ በምሥራቅ ካሉ ሰዎች ሁሉ ጥበብና ከግብጽ ጥበብ ሁሉ በለጠ።

Ver Capítulo



1 ነገሥት 4:30
14 Referencias Cruzadas  

አብ​ር​ሃ​ምም ለቁ​ባ​ቶቹ ልጆች ሀብ​ትን ሰጣ​ቸው፤ እር​ሱም ገና በሕ​ይ​ወቱ ሳለ ከልጁ ከይ​ስ​ሐቅ ለይቶ ወደ ምሥ​ራቅ ሀገር ሰደ​ዳ​ቸው።


ያዕ​ቆ​ብም በማ​ለዳ ተነ​ሥቶ የያ​ዕ​ቆ​ብና የዔ​ሳው እናት የር​ብቃ ወን​ድም የሶ​ርያ ሰው የባ​ቱ​ኤል ልጅ ወደ​ሚ​ሆን ወደ ላባ ሄደ።


ንጉ​ሡም ሰሎ​ሞን በብ​ል​ጥ​ግ​ናና በጥ​በብ ከም​ድር ነገ​ሥ​ታት ሁሉ እጅግ በልጦ ነበር።


ከብ​ቶ​ቹም፦ ሰባት ሺህ በጎች፥ ሦስት ሺህ ግመ​ሎች፥ አም​ስት መቶም ጥማድ በሬ፥ አም​ስት መቶም እን​ስት አህ​ዮች ነበሩ፤ እጅግ ብዙም አገ​ል​ጋ​ዮች ነበ​ሩት፤ ሥራ​ውም በም​ድር ላይ ታላቅ ነበረ፤ ያም ሰው በም​ሥ​ራቅ ካሉ ሰዎች ሁሉ ይልቅ ገናና ነበረ።


እኔ በልቤ፥ “እነሆ፥ ከእኔ አስ​ቀ​ድ​መው በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ላይ ከነ​በ​ሩት ሁሉ ይልቅ ጥበ​ብን አበ​ዛሁ፤ ልቤ​ንም ለጥ​በ​ብና ለዕ​ው​ቀት ሰጠሁ፥” በማ​ለት ተና​ገ​ርሁ።


ስለ​ዚህ እነሆ ርስት አድ​ርጌ ለም​ሥ​ራቅ ልጆች አሳ​ልፌ እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም ማደ​ሪ​ያ​ዎ​ቻ​ቸ​ውን በአ​ንተ ዘንድ ይሠ​ራሉ፤ ድን​ኳ​ኖ​ቻ​ቸ​ው​ንም በአ​ንተ ውስጥ ይተ​ክ​ላሉ፤ ፍሬ​ህን ይበ​ላሉ፤ ወተ​ት​ህ​ንም ይጠ​ጣሉ።


ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ ሰገል “የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና” እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ።


ከዚህ በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደ ተሣለቁበት ባየ ጊዜ እጅግ ተቆጣና ልኮ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ የነበሩትን፥ ሁለት ዓመት የሆናቸውን ከዚያም የሚያንሱትን ሕፃናት ሁሉ አስገደለ።


ሙሴም የግ​ብ​ፅን ጥበብ ሁሉ ተማረ፤ በሚ​ና​ገ​ረ​ውና በሚ​ሠ​ራ​ውም ሁሉ ብርቱ ሆነ።


ምድ​ያ​ምና አማ​ሌ​ቅም ሁሉ፥ የም​ሥ​ራ​ቅም ልጆች አንድ ሆነው ተሰ​በ​ሰቡ፤ ተሻ​ግ​ረ​ውም በኢ​ይ​ዝ​ራ​ኤል ሸለቆ ሰፈሩ።