እነዚህ እንግዲህ በባልና በሚስት፣ በአባትና ዐብራው በቤት ውስጥ በምትኖር ልጁ መካከል ያለውን ግንኙነት አስመልክቶ እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው ሥርዐቶች ናቸው።
ዘኍል 31:21 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም ከዚያም ካህኑ አልዓዛር ወደ ጦርነት ሄደው የነበሩትን ወታደሮች እንዲህ አላቸው፤ “እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው የሕጉ ሥርዐት ይህ ነው፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ካህኑም አልዓዛር ከጦርነት የተመለሱትን ወታደሮች እንዲህ አለ፦ “ጌታ ሙሴን ያዘዘው የሕጉ ሥርዓት ይህ ነው፤ አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ካህኑ አልዓዛር ከዘመቻ ለተመለሱት ወንዶች እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው የሕጉ ሥርዓት መመሪያዎች እነዚህ ናቸው፦ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ካህኑም አልዓዛር ከሰልፍ የመጡትን ሰዎች አላቸው፥ “እግዚአብሔር ሙሴን ያዘዘው የሕጉ ሥርዐት ይህ ነው፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ካህኑም አልዓዛር ከሰልፍ የመጡትን ሰዎች አላቸው፦ እግዚአብሔር ሙሴን ያዘዘው የሕጉ ሥርዓት ይህ ነው፤ |
እነዚህ እንግዲህ በባልና በሚስት፣ በአባትና ዐብራው በቤት ውስጥ በምትኖር ልጁ መካከል ያለውን ግንኙነት አስመልክቶ እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው ሥርዐቶች ናቸው።