ዘሌዋውያን 23:35 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በመጀመሪያው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ ይሁን፤ የጉልበት ሥራ ሁሉ አትሥሩበት። አዲሱ መደበኛ ትርጒም የመጀመሪያው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ ነውና የተለመደ ተግባራችሁን አታከናውኑበት። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከእነዚህም ቀኖች በመጀመሪያው ዕለት እግዚአብሔርን የምታመልኩበት በዓል ይሁን እንጂ ምንም ሥራ አትሥሩበት፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የመጀመሪያዋ ቀን ቅድስት ጉባኤ ትሁንላችሁ፤ የተግባር ሥራ ሁሉ አታድርጉባት። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በመጀመሪያው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ ይሁን፤ የተግባር ሥራ ሁሉ አታድርጉበት። |