ዘፍጥረት 49:14 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ይሳኮር አጥንተ ብርቱ አህያ ነው፥ በበጎች ጉረኖም መካከል ያርፋል። አዲሱ መደበኛ ትርጒም “ይሳኮር፣ በበጎች ጕረኖም መካከል የሚተኛ ዐጥንተ ብርቱ አህያ ነው። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም “ይሳኮር በበጎች መካከል እንደሚተኛ ብርቱ አህያ ነው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) “ይሳኮር መልካም ነገርን ወደደ፤ በተወራራሾቹም መካከል ያርፋል። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ይሳኮር አጥንተ ብርቱ አህያ ነው በበጎች ጕረኖም መካከል ያርፋል |
እስራኤልም የሚገባውን እንዲፈጽም የዘመኑን ሁኔታ የሚያውቁ ጥበበኞች ሰዎች የይሳኮር ልጆች አለቆች ሁለት መቶ ነበሩ፤ ወንድሞቻቸውም ሁሉ ይታዘዙአቸው ነበር።
ከአቤሜሌክ በኋላ ከይሳኮር ነገድ የሆነ የዱዲ ልጅ፥ የፎሖ ልጅ ቶላ እስራኤልን ለማዳን ተነሣ፤ እርሱም በኰረብታማው በኤፍሬም አገር ሳምር በምትባል መንደር ይኖር ነበር።