ዐይኖችህም አቅንተው ይዩ፥ ሽፋሽፍቶችህም ወደ እውነት ያመልክቱ።
ዐይኖችህ በቀጥታ ይመልከቱ፤ ትክ ብለህም ፊት ለፊት እይ።
ዐይኖችህ አቅንተው ይዩ፥ አተኩረው ፊት ለፊት ይመልከቱ።
አመለካከትህ ቀጥተኛ ይሁን፤ ግራና ቀኝ ሳትል ወደፊት ተመልከት።
“ከዐይኔ ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ፥ ድንግሊቱንም አልተመለከትሁም፤
የአላዋቂ ሰው መንገዶች ጠማሞች ናቸው፤ ብልህ ሰው ግን አቅንቶ ይሄዳል።
ኃጥእ ሰው ያለ ኀፍረት ፊት ለፊት ይቃወማል፤ ቅን ሰው ግን መንገዱን ይረዳል።
ዐይኖችህ ጋለሞታዎችን ያያሉ፥ ያንጊዜም አፍህ ጠማማ ነገርን ይናገራል።
በእርሱ ላይ ዐይንህን ብታተኩር አታገኘውም፥ ለእርሱ የንስር ክንፍ ተዘጋጅቶለታልና። ወደሚቆምበትም ቤት ይመለሳልና።
ክፉ አፍን ከአንተ አርቅ፥ ሐሰተኞች ከንፈሮችንም ከአንተ አስወግድ።
ለእግርህ ቀና መሄጃ ሥራ፥ መንገዶችህንም አቅና።
“የሰውነት መብራት ዐይን ናት። ዐይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤