La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




መሳፍንት 15:5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ችቦ​ው​ንም አን​ድዶ በቆ​መው በፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን እህል መካ​ከል ሰደ​ዳ​ቸው፤ ነዶ​ው​ንም፥ ክም​ሩ​ንም፥ የቆ​መ​ዉ​ንም እህል፥ ወይ​ኑ​ንም፥ ወይ​ራ​ዉ​ንም አቃ​ጠለ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ችቦውን በእሳት አቀጣጥሎ ቀበሮቹን በፍልስጥኤማውያን የእህል አዝመራ ላይ ለቀቃቸው፤ ነዶውንና የቆመውን አዝመራ እንዲሁም የወይኑንና የወይራውን ተክል አቃጠለ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ችቦውን በእሳት አቀጣጥሎ ቀበሮቹን በፍልስጥኤማውያን የእህል አዝመራ ላይ ለቀቃቸው፤ ነዶውንና የቆመውን አዝመራ እንዲሁም የወይኑንና የወይራውን ተክል አቃጠለ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ከዚያም በኋላ በችቦዎቹ ላይ እሳት በማቀጣጠል ቀበሮዎቹን ገና ወዳልታጨደው ወደ ፍልስጥኤማውያን የስንዴ ሰብል ውስጥ ለቀቃቸው፤ በዚህም ዐይነት ታጭዶ የተከመረውን ብቻ ሳይሆን ገና በማሳ ላይ ያለውን ስንዴ፥ የወይራና የወይን ተክል ጭምር አቃጠለ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ችቦውንም አንድዶ በቆመው በፍልስጥኤማውያን እህል መካከል ሰደዳቸው፥ ነዶውንም የቆመውንም እህል ወይኑንም ወይራውንም አቃጠለ።

Ver Capítulo



መሳፍንት 15:5
5 Referencias Cruzadas  

አቤ​ሴ​ሎ​ምም ብላ​ቴ​ኖ​ቹን፥ “በእ​ር​ሻዬ አጠ​ገብ ያለ​ች​ውን የኢ​ዮ​አ​ብን እርሻ እዩ፤ በዚ​ያም ገብስ አለው፤ ሄዳ​ችሁ በእ​ሳት አቃ​ጥ​ሉት” አላ​ቸው። የአ​ቤ​ሴ​ሎ​ምም ብላ​ቴ​ኖች እር​ሻ​ውን አቃ​ጠ​ሉት። የኢ​ዮ​አ​ብም አሽ​ከ​ሮች ልብ​ሶ​ቻ​ቸ​ውን ቀድ​ደው ተመ​ል​ሰው፥ “የአ​ቤ​ሴ​ሎም አሽ​ከ​ሮች እር​ሻ​ህን በእ​ሳት አቃ​ጠ​ሉት” ብለው ነገ​ሩት።


“እሳት ቢነሣ ጫካ​ው​ንም ቢይዝ፥ ዐው​ድ​ማ​ው​ንም፥ ክም​ሩ​ንም ወይም ያል​ታ​ጨ​ደ​ውን እህል ወይም እር​ሻ​ውን ቢያ​ቃ​ጥል እሳ​ቱን ያነ​ደ​ደው ይክ​ፈል።


በሰ​ባ​ተ​ኛው ዓመት ግን ተዋት፤ አሳ​ር​ፋ​ትም፤ የሕ​ዝ​ብ​ህም ድሆች ይበ​ሉ​ታል፤ እነ​ርሱ ያስ​ቀ​ሩ​ት​ንም የሜዳ እን​ስሳ ይብ​ላው። እን​ዲ​ሁም በወ​ይ​ን​ህና በወ​ይ​ራህ አድ​ርግ።


ሶም​ሶ​ንም ሄዶ ሦስት መቶ ቀበ​ሮ​ችን ያዘ፤ ችቦም ወስዶ ሁለት ሁለ​ቱን ቀበ​ሮ​ዎች በጅ​ራ​ታ​ቸው አሰረ፤ በሁ​ለ​ቱም ጅራ​ቶች መካ​ከል አንድ ችቦ አደ​ረገ።


ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም፥ “ይህን ያደ​ረገ ማን ነው?” አሉ። እነ​ር​ሱም፥ “ሚስ​ቱን ወስዶ ለሚ​ዜው አጋ​ብ​ቶ​በ​ታ​ልና የቴ​ም​ና​ታ​ዊዉ አማች ሶም​ሶን ነው” አሉ​አ​ቸው። ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም ወጥ​ተው የአ​ባ​ቷን ቤትና እር​ስ​ዋን አባ​ቷ​ንም በእ​ሳት አቃ​ጠሉ።