Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽሐፈ ጥበብ 15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


እው​ነ​ተ​ኛ​ውን አም​ላክ የማ​ም​ለክ ጥቅም

1 አንተ ፈጣ​ሪ​ያ​ችን ግን ቸር፥ እው​ነ​ተኛ፥ ታጋ​ሽም ነህ፥ በም​ሕ​ረ​ት​ህም ሁሉን ትሠ​ራ​ለህ።

2 ኀይ​ል​ህን እያ​ወ​ቅን ብን​በ​ድል፥ ያንተ መሆ​ና​ች​ንን እያ​ወ​ቅ​ንም ባን​በ​ድል ያንተ ነን።

3 አን​ተን ማወቅ ፍጽ​ምት ጽድቅ ናትና፥ ኀይ​ል​ህ​ንም ማወቅ የሕ​ይ​ወት ሥር ናትና።

4 ክፉ ዐሳብ፥ የሰው ጥበብ፥ ፍሬ የሌ​ለው የማ​ስ​ጌጥ ድካም፥ ወይም ቀለም በመ​ቀ​ባት መል​ካ​ቸው የሚ​ለ​ወጥ ሥራ​ዎች አያ​ስ​ቱ​ን​ምና።

5 የእ​ነ​ዚ​ህም መል​ካ​ቸው እነ​ር​ሱን ወደ መመ​ኘት ይመጣ ዘንድ አላ​ዋ​ቂን ሰው ይስ​በ​ዋል፤ ነፍ​ስና መን​ቀ​ሳ​ቀስ የሌ​ለው ምውት ጣዖ​ት​ንም ያስ​ወ​ድ​ደ​ዋል።

6 የሚ​ሠ​ሯ​ቸው የሚ​ወ​ዷ​ቸ​ውና የሚ​ያ​መ​ል​ኳ​ቸ​ውም ክፋ​ትን የሚ​ወ​ድዱ ናቸው። እን​ደ​ዚ​ህም የሚ​ያ​ደ​ርጉ በእ​ነ​ርሱ ላይ ተስፋ ያደ​ር​ጋሉ።


የሸ​ክላ ጣዖ​ትን የማ​ም​ለክ ሞኝ​ነት

7 ሸክላ ሠሪ ለስ​ላሳ አፈ​ርን በለ​ወሰ ጊዜ ከእኛ ለእ​ያ​ን​ዳ​ንዱ ሁሉ ሊያ​ገ​ለ​ግል የሚ​ገ​ባ​ውን የተ​ለ​ያየ ሥራን ይሠ​ራል፥ ነገር ግን ከዚ​ያው ጭቃ ለን​ጹሕ ሥራ አገ​ል​ግ​ሎት ዕቃ​ዎ​ችን ይሠ​ራል፥ እን​ደ​ዚ​ሁም ለሌ​ሎች ሥራ​ዎች በእ​ነ​ዚህ አም​ሳል ይሠ​ራል፤ የእ​ነ​ዚ​ህም ሁሉ ተግ​ባር ለተ​ለ​ያየ መፍ​ቅድ ነው፥ ነገር ግን ይህ ወይም ያ ለምን ጥቅም እን​ደ​ሚ​ውል ፈራጁ ዳኛ ሸክላ ሠሪው ነው።

8 ለክ​ፋት የሚ​ደ​ክም ሰው ግን ከዚያ ጭቃ ከንቱ ጣዖ​ትን ይሠ​ራል፥ ይህም ከጥ​ቂት ቀን አስ​ቀ​ድሞ ከም​ድር ተሠራ፤ ከጥ​ቂት ቀንም በኋላ ከእ​ርሷ ወደ ወጣ​ባት ምድር ይመ​ለስ ዘንድ አለው፥ ስለ ነፍሱ ፍር​ድም ይመ​ረ​መ​ራል።

9 በእ​ር​ሱም ዘንድ ያለው ትጋት ይሠ​ራና ይደ​ክም ዘንድ ስላ​ለ​ውና ሕይ​ወ​ቱም ጥቂት ስለ​ሆነ አይ​ደ​ለም። ወር​ቅና ብርን የሚ​ሠሩ ሰዎ​ችን ይፎ​ካ​ከ​ራ​ቸው ዘንድ ነው እንጂ፤ ናስ ሠሪ​ዎ​ች​ንም ይመ​ስ​ላ​ቸው ዘንድ ነው እንጂ፥ የተ​ዋ​ረ​ደ​ው​ንም ሠርቶ ክብር ይሰ​ጠ​ዋል።

10 ልቡ​ናው አመድ ነው፥ ተስ​ፋ​ውም ከአ​ፈር ይጐ​ሰ​ቍ​ላል፥ ሕይ​ወ​ቱም ከጭቃ እጅግ የተ​ናቀ ነው።

11 የፈ​ጠ​ረ​ው​ንና ነባ​ቢት ነፍ​ስን ያሳ​ደ​ረ​በ​ትን፥ የሕ​ይ​ወት መን​ፈ​ስ​ንም እፍ ያለ​በ​ትን አላ​ወ​ቀ​ው​ምና።

12 ነገር ግን እነ​ዚህ ሕይ​ወ​ታ​ች​ንን ጨዋ​ታና መዘ​ባ​በቻ አድ​ር​ገው ዐሰቡ፥ ኑሯ​ች​ን​ንም የት​ርፍ ምል​ክት አደ​ረ​ጉት፤ ስላ​ጣሁ ይጨ​ን​ቀ​ኛል ብሏ​ልና፥ ከዚ​ህም በኋላ ያተ​ር​ፋል፥ ክፋ​ት​ንም ገን​ዘብ ያደ​ር​ጋል።

13 ይህም ከሁሉ ፈጽሞ እን​ደ​ሚ​በ​ድል ታወቀ፥ በም​ድር ከሚ​ታ​የ​ውና ፈጥኖ ከሚ​ጠ​ፋው ከእ​ን​ጨት የተ​ቀ​ረፀ ጣዖ​ትን ሠር​ት​ዋ​ልና።

14 ሁሉም አላ​ዋ​ቂ​ዎ​ችና ጐስ​ቋ​ሎች ናቸው፥ ሁሉም ከተ​ማ​ረኩ ወገ​ኖች ተለ​ይ​ተው ሙታን ናቸው፥ በእ​ርሱ የታ​ሰ​ሩም ሰዎች ከሕ​ፃ​ናት ሰው​ነት ይልቅ ስን​ፍ​ናን ያበ​ዛሉ።

15 መሥ​ራት የማ​ይ​ቻ​ላ​ቸው፥ በዐ​ይ​ና​ቸው ማየት፥ ባፍ​ን​ጫ​ቸው ነፋ​ስን ማሽ​ተት፥ በጆ​ሮ​አ​ቸ​ውም መስ​ማት፥ በእ​ጆ​ቻ​ቸው ጣቶች መዳ​ሰስ የማ​ይ​ቻ​ላ​ቸው፥ እግ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም ከመ​ሄድ የቦ​ዘኑ የአ​ሕ​ዛ​ብን ጣዖ​ቶች አማ​ል​ክት አድ​ር​ገው ዐስ​በ​ዋ​ልና።

16 ሰው ሠር​ት​ዋ​ቸ​ዋ​ልና፥ መን​ፈስ የተ​ከ​ፈ​ለ​ውም ሰው ቀር​ፆ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ ራሱን አስ​መ​ስሎ አም​ላ​ክን ይሠራ ዘንድ ለሰው አይ​ቻ​ለ​ው​ምና።

17 እርሱ መዋቲ ሲሆን በኀ​ጢ​አት እጅ መዋ​ቲን ይሠ​ራል፥ እርሱ ሕያው ስለ​ሆነ እነ​ዚህ ግን ከቶ ሕያ​ዋን ስላ​ይ​ደሉ ከጣ​ዖ​ቶቹ ይሻ​ላ​ልና።

18 እን​ስ​ሳ​ዎ​ች​ንም አማ​ል​ክት ያደ​ረ​ጓ​ቸው እነ​ዚህ በስ​ን​ፍና ያመ​ል​ኳ​ቸ​ዋል፥ እነ​ዚ​ህን ግን በሕ​ሊና ቢመ​ዝ​ኗ​ቸው ከሌ​ሎች አማ​ል​ክት ይከ​ፋሉ።

19 ምኞ​ትን የወ​ደ​ደም እን​ስ​ሳ​ትን በማ​የት ከእ​ነ​ርሱ በአ​ንዱ ምኞ​ቱን ፈጸመ፥ በአ​ን​ዱም በደለ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋ​ናና ክብር በዚህ ርቋ​ልና።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos