Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ዘሌዋውያን 18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የተ​ከ​ለ​ከለ ሩካቤ

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን እን​ዲህ ብሎ ተና​ገ​ረው፦

2 “ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እን​ዲህ ብለህ ንገ​ራ​ቸው፦ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝ።

3 እንደ ተቀ​መ​ጣ​ች​ሁ​ባት እንደ ግብፅ ምድር ሥራ አት​ሥሩ፤ እኔም ወደ እር​ስዋ እን​ደ​ማ​ገ​ባ​ችሁ እንደ ከነ​ዓን ምድር ሥራ አት​ሥሩ፤ በሥ​ር​ዐ​ታ​ቸ​ውም አት​ሂዱ።

4 ፍር​ዴን አድ​ርጉ፤ በእ​ር​ስ​ዋም ትሄዱ ዘንድ ሥር​ዐ​ቴን ጠብቁ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝ።

5 የሚ​ሠ​ራ​ቸው ሰው በእ​ነ​ርሱ በሕ​ይ​ወት ይኖ​ራ​ልና ሥር​ዐ​ቴ​ንና ፍር​ዴን ጠብቁ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝ።

6 “ከእ​ና​ን​ተም ማንም ሰው ኀፍ​ረተ ሥጋ​ውን ይገ​ልጥ ዘንድ ወደ ሥጋ ዘመዱ ሁሉ አይ​ቅ​ረብ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝ።

7 የአ​ባ​ት​ህን ኀፍ​ረተ ሥጋና የእ​ና​ት​ህን ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ እና​ትህ ናትና ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን አት​ግ​ለጥ።

8 የአ​ባ​ት​ህን ሚስት ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የአ​ባ​ትህ ኀፍ​ረተ ሥጋ ነው።

9 የእ​ኅ​ት​ህን ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የአ​ባ​ትህ ልጅ ወይም የእ​ና​ትህ ልጅ በቤት ወይም በውጭ የተ​ወ​ለ​ደች ብት​ሆን፥ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን አት​ግ​ለጥ።

10 የወ​ንድ ልጅ​ህን ሴት ልጅ ኀፍ​ረተ ሥጋ ወይም የሴት ልጅ​ህን ሴት ልጅ ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የአ​ንተ ኀፍ​ረተ ሥጋ ነውና።

11 ከአ​ባ​ትህ የተ​ወ​ለ​ደ​ች​ውን የአ​ባ​ት​ህን ሚስት ልጅ ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ ከአ​ባ​ትህ የተ​ወ​ለ​ደች እኅ​ትህ ናት፤ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን አት​ግ​ለጥ።

12 የአ​ባ​ት​ህን እኅት ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የአ​ባ​ትህ ዘመድ ናትና።

13 የእ​ና​ት​ህን እኅት ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የእ​ና​ትህ ዘመድ ናትና።

14 የአ​ባ​ት​ህን ወን​ድም ሚስት ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ ዘመ​ድህ ናትና።

15 የም​ራ​ት​ህን ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የል​ጅህ ሚስት ናት፤ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን አት​ግ​ለጥ።

16 የወ​ን​ድ​ም​ህን ሚስት ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የወ​ን​ድ​ምህ ኀፍ​ረተ ሥጋ ነውና።

17 የሴ​ት​ንና የሴት ልጅ​ዋን ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የወ​ንድ ልጅ​ዋን ሴት ልጅ ወይም የሴት ልጅ​ዋን ሴት ልጅ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን ትገ​ልጥ ዘንድ አታ​ግባ፤ ዘመ​ዶች ናቸው፤ ኀጢ​አት ነውና።

18 በእ​ኅቷ ላይ እን​ዳ​ት​ቀና ሚስ​ትህ በሕ​ይ​ወት ሳለች የእ​ኅ​ቷን ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ።

19 “እር​ስ​ዋም በግ​ዳ​ጅዋ ርኵ​ሰት ሳለች ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋን ትገ​ልጥ ዘንድ ሳት​ነጻ በግ​ዳ​ጅዋ ወደ አለች ሴት አት​ቅ​ረብ።

20 ከባ​ል​ን​ጀ​ራህ ሚስት ጋር አት​ተኛ፤ ዘር​ህ​ንም አት​ዝ​ራ​ባት።

21 ከዘ​ር​ህም ለሞ​ሎክ አት​ስጥ የአ​ም​ላ​ክ​ህ​ንም ስም አታ​ር​ክስ፤ እኔ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነኝ።

22 ከሴ​ትም ጋር እን​ደ​ም​ት​ተኛ ከወ​ንድ ጋር አት​ተኛ፤ ጸያፍ ነገር ነውና።

23 ዘር​ህን በእ​ር​ስዋ ላይ እን​ዳ​ት​ዘ​ራና እን​ዳ​ት​ረ​ክ​ስ​ባት ወደ እን​ስሳ አት​ሂድ፤ ሴት ከእ​ርሱ ጋር ትተኛ ዘንድ በእ​ን​ስሳ ፊት አት​ቁም፤ የተ​ጠላ ነገር ነውና።

24 “ከፊ​ታ​ችሁ የማ​ሳ​ድ​ዳ​ቸው አሕ​ዛብ በእ​ነ​ዚህ ሁሉ ረክ​ሰ​ዋ​ልና በእ​ነ​ዚህ ነገ​ሮች ሁሉ አት​ር​ከሱ።

25 ምድ​ሪ​ቱም ረከ​ሰች፤ ስለ​ዚህ ኀጢ​አ​ቷን በእ​ር​ስዋ ላይ እመ​ል​ሳ​ለሁ፤ ምድ​ሪ​ቱም የሚ​ኖ​ሩ​ባ​ትን ሰዎች ትተ​ፋ​ለች።

26 ሥር​ዐ​ቴ​ንና ፍር​ዴን ጠብቁ፤ እና​ን​ተም የሀ​ገሩ ልጆች፥ በእ​ና​ን​ተም መካ​ከል የሚ​ኖ​ሩት እን​ግ​ዶች ከዚህ ርኵ​ሰት ምንም አት​ሥሩ፤

27 ከእ​ና​ንተ በፊት የነ​በ​ሩት የሀ​ገሩ ልጆች ይህን ርኵ​ሰት ሁሉ ሠር​ተ​ዋ​ልና፥ ምድ​ሪ​ቱ​ንም አር​ክ​ሰ​ዋ​ታ​ልና፤

28 ምድ​ሪ​ቱም ከእ​ና​ንተ በፊት የነ​በ​ረ​ውን ሕዝብ እንደ ተፋች ባረ​ከ​ሳ​ች​ኋት ጊዜ እና​ን​ተ​ንም እን​ዳ​ት​ተ​ፋ​ችሁ ተጠ​ን​ቀቁ።

29 ከዚህ ርኵ​ሰት ሁሉ ማና​ቸ​ውን የሚ​ያ​ደ​ርግ ያ ሰው ከሕ​ዝቡ መካ​ከል ተለ​ይቶ ይጠ​ፋ​ልና።

30 ስለ​ዚህ ከእ​ና​ንተ በፊት የነ​በሩ ሰዎች የሠ​ሩ​ትን ጸያፍ የሆ​ነ​ውን ወግ ሁሉ እን​ዳ​ት​ሠሩ፥ በእ​ር​ሱም እን​ዳ​ት​ረ​ክሱ ሥር​ዐ​ቴን ጠብቁ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝና።”

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos