ዋጋው ብዙ ከሆነ ዕንቍም የከበረች ናት። ክፉ ነገር አይቃወማትም፥ ለሚቀርቧትም መልካም ናት። ክብርም ሁሉ አይተካከላትም።
ከቀይ ዕንቍ ይበልጥ ውድ ናት፤ አንተ ከምትመኘውም ሁሉ የሚስተካከላት የለም።
ከውድ ዕንቁም ትከብራለች፥ ከምትመኘው ነገር አንዳችም አይተካከላትም።
ጥበብ ከውድ ዕንቊ ትከብራለች፤ አንተ ለማግኘት ከምትመኛቸው ነገሮች ሁሉ እርስዋን የሚወዳደራት ከቶ የለም።
ዛጎልና አልማዝ አይታሰቡም። አንተ ግን እጅግ ከከበሩ ነገሮች ሁሉ ይልቅ ጥበብን አቅርባት።
እንደ እባብ ምላሳቸውን አሰሉ፤ መራራ ነገርን ለማድረግ፥
ወርቅና ብዙ ቀይ ዕንቍ ይገኛል፤ የዕውቀት ከንፈር ግን የከበረች ጌጥ ናት።
ከብር ይልቅ ትምህርትን፥ ከተፈተነ ወርቅም ይልቅ ዕውቀትን ተቀበሉ።
ዋጋው ብዙ ከሆነ ዕንቍ ጥበብ ትበልጣለችና፥ የከበረ ነገር ሁሉ አይተካከላትም።
ጥበብ ከርስት ጋር መልካም ነው፤ ፀሓይንም ለሚያዩ ሰዎች ትርፍን ይሰጣል።
ነገር ግን የዚህ ዓለም መከራ ለእና ሊገለጥ ከአለው ክብር ጋር እንደማይተካከል ዐስቡ።