Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


መዝሙር 63 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለመ​ዘ​ም​ራን አለቃ የዳ​ዊት መዝ​ሙር።

1 አቤቱ፥ ወደ አንተ የለ​መ​ን​ሁ​ትን ጸሎ​ቴን ስማኝ፥ ከጠ​ላ​ትም ጥር​ጥር ነፍ​ሴን አድ​ናት።

2 ከክ​ፉ​ዎች ሴራ ከብ​ዙ​ዎች ዐመፅ አድ​ራ​ጊ​ዎች ሰው​ረኝ።

3 እንደ እባብ ምላ​ሳ​ቸ​ውን አሰሉ፤ መራራ ነገ​ርን ለማ​ድ​ረግ፥

4 ንጹ​ሕ​ንም በስ​ውር ለመ​ግ​ደል ቀስ​ትን ገተሩ፤ በድ​ን​ገት ይነ​ድ​ፏ​ቸ​ዋል አይ​ፈ​ሩ​ምም።

5 ለእ​ነ​ርሱ ለራ​ሳ​ቸው ክፉ ነገ​ርን አጸኑ፤ ወጥ​መ​ድን ይሰ​ውሩ ዘንድ ተማ​ከሩ፤ የሚ​ያ​ም​ንም የለም ይላሉ።

6 ዐመ​ፃን ፈለ​ጓት፥ ሲፈ​ት​ኑም ሲጀ​ም​ሩም አለቁ፤ ሰው በጥ​ልቅ ልብ ውስጥ ይገ​ባል፥

7 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከፍ ከፍ ይላል። መቅ​ሠ​ፍ​ታ​ቸው እንደ ልጆች ሕንፃ ሆነ፤

8 አን​ደ​በ​ታ​ቸው በላ​ያ​ቸው ደከመ፥ የሚ​ያ​ዩ​አ​ቸ​ውም ሁሉ ደነ​ገጡ።

9 ሰው ሁሉ ፈራ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሥራ ተና​ገሩ፥ ሥራ​ው​ንም ዐወቁ።

10 ጻድቅ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ደስ ይለ​ዋል፥ በእ​ር​ሱም ይታ​መ​ናል፤ ልባ​ቸ​ውም የቀና ሁሉ ይከ​ብ​ራሉ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos