La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘኍል 35:3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ከተ​ሞ​ቹም ለእ​ነ​ርሱ መኖ​ሪያ ይሆ​ናሉ፤ መሰ​ማ​ር​ያ​ቸ​ውም ለከ​ብ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ለእ​ን​ስ​ሶ​ቻ​ቸው ይሁን።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ከተሞቹ ለእነርሱ መኖሪያ፣ የግጦሽ መሬቱ ለከብቶቻቸው፣ ለበግና ለፍየል መንጎቻቸውና ለሌሎቹም እንስሶቻቸው ይሆናሉ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እንዲቀመጡባቸውም ከተሞቹ ለእነርሱ ይሆናሉ፤ መሰማሪያቸውም ለከብቶቻቸው ለእንስሶቻቸውም እነርሱም ላሏቸው ነገሮች ሁሉ ይሁን።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

እነዚህም ከተሞች የሌዋውያን ይዞታ ሆነው እነርሱ ይኖሩባቸዋል፤ የግጦሽ መሬቱም ለከብቶቻቸውና ለሌሎች እንስሶቻቸው ይሆናል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

እነርሱም በከተሞቹ ውስጥ ይቀመጣሉ፤ መሰምርያቸውም ለከብቶቻቸው ለእንስሶቻቸውም ለእነርሱም ላለው ሁሉ ይሁን።

Ver Capítulo



ዘኍል 35:3
6 Referencias Cruzadas  

የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ካህ​ናት እን​ዳ​ይ​ሆኑ ኢዮ​ር​ብ​ዓ​ምና ልጆቹ አስ​ለ​ቅ​ቀ​ዋ​ቸው ነበ​ርና ሌዋ​ው​ያን መሰ​ም​ሪ​ያ​ቸ​ውን ትተው ወደ ይሁ​ዳና ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም መጡ።


ከእ​ር​ሱም ርዝ​መቱ አም​ስት መቶ፥ ወር​ዱም አም​ስት መቶ ክንድ አራት ማዕ​ዘን የሆነ ቦታ ለመ​ቅ​ደሱ ይሆ​ናል፤ በዙ​ሪ​ያ​ውም ባዶ ስፍራ የሚ​ሆን አምሳ ክንድ ይሆ​ናል።


“ሌዋ​ው​ያን የሚ​ቀ​መ​ጡ​ባ​ቸ​ውን ከተ​ሞች ከሚ​ካ​ፈ​ሉት ርስ​ታ​ቸው ይሰጡ ዘንድ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እዘ​ዛ​ቸው፤ በከ​ተ​ሞ​ቹም ዙሪያ ያሉ​ትን መሰ​ማ​ሪ​ያ​ዎች ለሌ​ዋ​ው​ያን ይስ​ጡ​አ​ቸው።


ለሌ​ዋ​ው​ያ​ንም የም​ት​ሰ​ጡት የከ​ተማ መሰ​ማ​ርያ በከ​ተ​ማው ዙሪያ ከቅ​ጥሩ ወደ ውጭ አንድ ሺህ ክንድ ይሁን።


“አንድ ሌዋዊ ሰው ከሚ​ቀ​መ​ጥ​ባ​ቸው በእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ዘንድ ካሉት ከተ​ሞች ከአ​ን​ዲቱ፥ በፍ​ጹም ልብም ሊያ​ገ​ለ​ግል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወደ መረ​ጠው ስፍራ ቢመጣ፥


የኤ​ናቅ ልጆች ከተማ ቅር​ያ​ት​ያ​ር​ቦ​ቅ​ንና በዙ​ሪ​ያዋ ያሉ መሰ​ማ​ሪ​ያ​ዎ​ችን ሰጡ​አ​ቸው፤ ይህ​ች​ውም በይ​ሁዳ ተራራ ያለች ኬብ​ሮን ናት።