“እናንተ የሌዋውያን አባቶች ቤቶች አለቆች ናችሁ፤ ወዳዘጋጀሁላት ስፍራ የእስራኤልን አምላክ የእግዚአብሔርን ታቦት ታመጡ ዘንድ እናንተና ወንድሞቻችሁ ተቀደሱ።
ነህምያ 12:12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በዮአቂምም ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቆች ወንድሞቹ ካህናቱ ነበሩ፤ ከሠራያ ምራያ፥ ከኤርምያስ ሐናንያ፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም በዮአቂም ዘመን የካህናቱ ቤተ ሰብ አለቆች እነዚህ ነበሩ፤ ከሠራያ ቤተ ሰብ፣ ምራያ፤ ከኤርምያስ፣ ሐናንያ፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በዮያቂም ዘመን የአባቶች መሪዎች ካህናቱ እነዚህ ነበሩ፦ ከሥራያ ቤተሰብ ምራያ፥ ከኤርምያስ ሐናንያ፥ አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ዮያቂም ሊቀ ካህናት በነበረበት ዘመን ከዚህ የሚከተሉት ካህናት፥ የካህናት ጐሣዎች አለቆች ነበሩ፦ ካህኑ ጐሣው። መራያ ሠራያ። ሐናንያ ኤርምያስ። መሹላም ዕዝራ። የሆሐናን አማርያ። ዮናታን መሉኪ። ዮሴፍ ሸካንያ። ዓድና ሓሪም። ሔልቃይ መራዮት። ዘካርያስ ዒዶ። መሹላም ጊነቶን። ዚክሪ አቢያ። ሚንያሚን ፒልጣይ ሞዓዲያ። ሻሙዐ ቢልጋ። የሆናታን ሸማዕያ። ማትናይ ዮያሪብ። ዑዚ ይዳዕያ። ቃላይ ሳላይ። ዔቤር ዓሞቅ። ሐሻብያ ሒልቂያ። ናትናኤል ይዳዕያ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በዮአቂምም ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቆች እነዚህ ካህናቱ ነበሩ፥ ከሠራያ ምራያ፥ |
“እናንተ የሌዋውያን አባቶች ቤቶች አለቆች ናችሁ፤ ወዳዘጋጀሁላት ስፍራ የእስራኤልን አምላክ የእግዚአብሔርን ታቦት ታመጡ ዘንድ እናንተና ወንድሞቻችሁ ተቀደሱ።
የአልዓዛርም ልጆች አለቆች ከኢታምር ልጆች አለቆች በልጠው ተገኙ፤ እንዲህም ተመደቡ፤ ከአልዓዛር ልጆች እንደ አባቶቻቸው ቤቶች ዐሥራ ስድስት አለቆች፥ ከኢታምርም ልጆች እንደ አባቶቻቸው ቤቶች ስምንት አለቆች ነበሩ።
ከሌዋውያኑም በኤልያሴብና በዮሐዳ፥ በዮሐናንና በያዱዕ ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቆች ተጻፉ፤ ካህናቱም በፋርሳዊው በዳርዮስ መንግሥት ዘመን ተጻፉ።