La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኢዩኤል 2:15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

በጽ​ዮን መለ​ከ​ትን ንፉ፤ ጾም​ንም ቀድሱ፤ ምህ​ላ​ንም ዐውጁ፤

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

በጽዮን መለከትን ንፉ፤ ቅዱስ ጾምን ዐውጁ፤ የተቀደሰን ጉባኤ ጥሩ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

በጽዮን መለከትን ንፉ፥ ጾምንም ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፥

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

በጽዮን ተራራ ላይ መለከት ንፉ! ሕዝቡን ለመንፈሳዊ ስብሰባ ጥሩ! ጾምንም ዐውጁ!

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

በጽዮን መለከትን ንፉ፥ ጾምንም ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፥

Ver Capítulo



ኢዩኤል 2:15
8 Referencias Cruzadas  

ከዚ​ህም በኋላ ይህን ነገር በሰማ ጊዜ አብ​ረ​ውት ካሉት ከነ​ገ​ሥ​ታቱ ሁሉ ጋር በድ​ን​ኳኑ ውስጥ ይጠጣ ነበር፤ አገ​ል​ጋ​ዮ​ቹ​ንም፥ “ከተ​ማ​ውን እጠ​ሩት” አላ​ቸው። እነ​ር​ሱም በከ​ተ​ማ​ዪቱ ትይዩ ተሰ​ለፉ።


ለወ​ልደ አዴር መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችም፥ “ለጌ​ታ​ችሁ፦ ለእኔ አገ​ል​ጋ​ይህ በመ​ጀ​መ​ሪያ የላ​ክ​ህ​ብ​ኝን ሁሉ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ ይህን ነገር ግን አደ​ር​ገው ዘንድ አይ​ቻ​ለ​ኝም” በሉት አላ​ቸው። መል​ክ​እ​ክ​ተ​ኞ​ችም ተመ​ል​ሰው ይህን ነገር ነገ​ሩት።


ኢዩም፥ “ለበ​ዓል መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ች​ሁን አንጹ” አላ​ቸው፤ እነ​ር​ሱም አዋጅ ነገሩ።


መል​ካ​ሙን የስ​ንዴ ዱቄት ብታ​መጡ እንኳ ከንቱ ነው፤ ዕጣ​ና​ችሁ በእኔ ዘንድ አስ​ጸ​ያፊ ነው፤ መባ​ቻ​ዎ​ቻ​ች​ሁ​ንና ሰን​በ​ቶ​ቻ​ች​ሁን፥ ታላ​ቋን፥ ቀና​ች​ሁን፥ ጾማ​ች​ሁ​ንና ሥራ መፍ​ታ​ታ​ች​ሁን አል​ወ​ድም።


እን​ዲ​ህም ሆነ፤ የይ​ሁዳ ንጉሥ የኢ​ዮ​ስ​ያስ ልጅ ኢዮ​አ​ቄም በነ​ገሠ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ዓመት በዘ​ጠ​ነ​ኛው ወር በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የተ​ቀ​መጡ ሕዝብ ሁሉ፥ ከይ​ሁ​ዳም ከተ​ሞች ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም የመጡ ሕዝብ ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ለመ​ጾም ዐዋጅ ነገሩ።


ጾምን ቀድሱ፤ ምህ​ላ​ንም ዐውጁ፤ ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ቹ​ንና በም​ድር የሚ​ኖ​ሩ​ትን ሁሉ ወደ አም​ላ​ካ​ችን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ሰብ​ስቡ፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በአ​ን​ድ​ነት ጩኹ።


በጽ​ዮን መለ​ከ​ትን ንፉ፤ በቅ​ዱ​ሱም ተራ​ራዬ ላይ ዐዋጅ ንገሩ፤ በም​ድ​ርም የሚ​ኖሩ ሁሉ ይደ​ን​ግጡ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀን መጥ​ቶ​አ​ልና፥ እር​ሱም ቀር​ቦ​አ​ልና።


ሁለ​ቱም መለ​ከ​ቶች በተ​ነፉ ጊዜ ማኅ​በሩ ሁሉ ወደ አንተ ወደ ምስ​ክሩ ድን​ኳን ይሰ​ብ​ሰቡ።