ዘፀአት 26:18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ለድንኳኑም በደቡብ በኩል ሃያ ሳንቆችን አድርግ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ለማደሪያው ድንኳን ክፍል በደቡብ በኩል ሃያ ወጋግራዎችን ሥራ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ለማደሪያውም በደቡብ ወገን ሀያ ሳንቃዎችን አድርግ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከድንኳኑ በስተ ደቡብ በኩል ኻያ ተራዳዎችን አድርግ፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ለማደሪያውም በደቡብ ወገን ሀያ ሳንቆችን አድርግ። |
ለእያንዳንዱም ሳንቃ አንዱን በአንዱ ላይ የሚያያይዙ ሁለት ማጋጠሚያዎች ይሁኑለት፤ ለድንኳኑ ሳንቆች ሁሉ እንዲሁ አድርግ።
ከሃያውም ሳንቆች በታች አርባ የብር እግሮችን አድርግ፤ ከእያንዳንዱ ሳንቃ በታች ለሁለት ማጋጠሚያዎች ሁለት እግሮች ይሁኑ። ከሌላውም ሳንቃ በታች ለሁለት ማጋጠሚያዎች ሁለት እግሮች ይሁኑ።