La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ዜና መዋዕል 13:20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ኢዮ​ር​ብ​ዓ​ምም ከዚያ በኋላ በአ​ብያ ዘመን አል​በ​ረ​ታም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቀሠ​ፈው፤ ሞተም።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ኢዮርብዓም በአብያ ዘመን እንደ ገና ሊያንሰራራ አልቻለም፤ ከዚያም እግዚአብሔር ስለ ቀሠፈው ሞተ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ኢዮርብዓምም ከዚያ በኋላ በአብያ ዘመን አልበረታም፤ ጌታም ቀሰፈው፥ ሞተም።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ከዚያም በኋላ ኢዮርብዓም በአቢያ ዘመነ መንግሥት ኀይሉን ሊያንሠራራ አልቻለም፤ በመጨረሻም እግዚአብሔር በሞት ቀሠፈው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ኢዮርብዓምም ከዚያ በኋላ በአብያ ዘመን አልበረታም፤ እግዚአብሔርም ቀሰፈው፤ ሞተም።

Ver Capítulo



2 ዜና መዋዕል 13:20
9 Referencias Cruzadas  

ኢዮ​ር​ብ​ዓ​ምም የነ​ገ​ሠ​በት ዘመን ሃያ አራት ዓመት ነበረ፥ ከአ​ባ​ቶ​ቹም ጋር አን​ቀ​ላፋ፥ ልጁም ናባጥ በፋ​ን​ታው ነገሠ።


በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ በኢ​ዮ​ር​ብ​ዓም በሃያ አራ​ተ​ኛው ዓመት አሳ በይ​ሁዳ ላይ ነገሠ።


አብ​ያም ኢዮ​ር​ብ​ዓ​ምን ተከ​ትሎ አሳ​ደ​ደው፤ ከእ​ር​ሱም ከተ​ሞ​ቹን ቤቴ​ል​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን፥ ይሳ​ና​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን፥ ዔፍ​ሮ​ን​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን ወሰደ።


አብ​ያም ጸና፤ ዐሥራ አራት ሚስ​ቶ​ች​ንም አገባ፤ ሃያ ሁለ​ትም ወን​ዶች ልጆ​ች​ንና ዐሥራ ስድ​ስት ሴቶች ልጆ​ችን ወለደ።


“የሰው ልጅ ሆይ! እነሆ የዐ​ይ​ን​ህን አም​ሮት በመ​ቅ​ሠ​ፍት እወ​ስ​ድ​ብ​ሃ​ለሁ፤ አን​ተም ዋይ አት​በል፤ አታ​ል​ቅ​ስም፤ እን​ባ​ህ​ንም አታ​ፍ​ስስ።


ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ክብር ስለ አል​ሰጠ ያን​ጊዜ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​አክ ቀሠ​ፈው፤ ተል​ቶም ሞተ።


ከዐ​ሥር ቀንም በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ናባ​ልን ቀሠ​ፈው፤ እር​ሱም ሞተ።


ደግ​ሞም ዳዊት አለው፥ “ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ካል​ገ​ደ​ለው፥ ወይም ቀኑ ደርሶ ካል​ሞተ፥ ወይም ወደ ጦር​ነት ወርዶ ካል​ሞተ እኔ አል​ገ​ድ​ለ​ውም።