La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




1 ሳሙኤል 6:14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ሰረ​ገ​ላ​ውም ወደ ቤት​ሳ​ሚ​ሳ​ዊው ወደ ኦሴዕ እርሻ መጣ፤ ታላ​ቅም ድን​ጋይ በነ​በ​ረ​በት በዚያ ቆመ፤ የሰ​ረ​ገ​ላ​ው​ንም ዕን​ጨት ፈል​ጠው ላሞ​ቹን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት አቀ​ረቡ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሠረገላውም ወደ ቤትሳሚስ ወደ ኢያሱ ዕርሻ መጥቶ በአንድ ትልቅ ቋጥኝ አጠገብ ቆመ። ሕዝቡም የሠረገላውን ዕንጨት ፈልጠው፣ ሁለቱን ላሞች የሚቃጠል መሥዋዕት አድርገው ለእግዚአብሔር አቀረቡ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ሠረገላውም ወደ ቤትሼሜሽ ወደ ኢያሱ እርሻ መጥቶ ቆመ። በዚያ ስፍራ አንድ ትልቅ ቋጥኝ ነበር። ሕዝቡም የሠረገላውን ዕንጨት ፈለጡት፤ ላሞቹንም የሚቃጠል መሥዋዕት አድርገው ለጌታ አቀረቡ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ሠረገላውም በቤትሼሜሽ ወደሚኖር ኢያሱ ተብሎ ወደሚጠራው ሰው እርሻ መጥቶ በትልቅ ቋጥኝ አጠገብ ሲደርስ ቆመ። ሕዝቡም የሠረገላውን እንጨት ፈለጡ፤ ላሞቹንም ዐርደው ለእግዚአብሔር የሚቃጠል መሥዋዕት አድርገው አቀረቡአቸው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ሰረገላውም ወደ ቤትሳሚሳዊው ወደ ኢያሱ እርሻ መጣ፥ ታላቅም ድንጋይ በነበረበት በዚያ ቆመ፥ የሰረገላውንም እንጨት ፈልጠው ላሞቹን ለእግዚአብሔር ለሚቃጠል መሥዋዕት አቀረቡ።

Ver Capítulo



1 ሳሙኤል 6:14
13 Referencias Cruzadas  

በዚ​ያም ቀን ጋድ ወደ ዳዊት መጥቶ፥ “ውጣ፤ በኢ​ያ​ቡ​ሳ​ዊው በኦ​ርና አው​ድማ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ ሥራ” አለው።


ኦር​ናም ዳዊ​ትን፥ “ጌታዬ ንጉሡ በፊቱ ደስ ያሰ​ኘ​ውን ወስዶ ያቅ​ርብ፤ እነ​ሆም፥ ለሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት በሬ​ዎች፥ ለሚ​ቃ​ጠ​ልም እን​ጨት የአ​ው​ድማ ዕቃና የበሬ ዕቃ አለ።


በዚ​ያም ዳዊት ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ ሠራ፤ የሚ​ቃ​ጠ​ልና የሰ​ላም መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም አቀ​ረበ። ሰሎ​ሞ​ንም በኋላ ዘመን በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ጨመረ፤ ያን​ጊዜ አነ​ስ​ተኛ ነበ​ርና። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስለ ሀገ​ሪቱ የተ​ለ​መ​ነ​ውን ሰማ፤ መቅ​ሠ​ፍ​ቱም ከእ​ስ​ራ​ኤል ተከ​ለ​ከለ።


ከእ​ር​ሱም ዘንድ ተመ​ልሶ ሁለ​ቱን በሬ​ዎች ወስዶ አረ​ዳ​ቸው፤ ሥጋ​ቸ​ው​ንም በበ​ሬ​ዎቹ ዕቃ ቀቀ​ለው፤ ለሕ​ዝ​ቡም ሰጣ​ቸው፤ በሉም፤ እር​ሱም ተነ​ሥቶ ኤል​ያ​ስን ተከ​ትሎ ሄደ፤ ያገ​ለ​ግ​ለ​ውም ነበር።


ከአ​ፈ​ርም መሠ​ዊያ ሥራ​ልኝ፤ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ው​ንና የደ​ኅ​ን​ነት መሥ​ዋ​ዕ​ት​ህን፥ በጎ​ች​ህ​ንም፥ በሬ​ዎ​ች​ህ​ንም ሠዋ​በት፤ ስሜን ባስ​ጠ​ራ​ሁ​በት ስፍራ ሁሉ ወደ አንተ መጥቼ እባ​ር​ክ​ሃ​ለሁ።


በነ​ጋ​ውም ሕዝቡ ማል​ደው ተነሡ፤ በዚ​ያም መሠ​ዊያ ሠሩ፤ የሚ​ቃ​ጠ​ልና የደ​ኅ​ን​ነት መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም አቀ​ረቡ።


በዚ​ያም ተራራ አናት ላይ ለአ​ም​ላ​ክህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ አሳ​ም​ረህ ሥራ፤ ሁለ​ተ​ኛ​ዉ​ንም በሬ ውሰድ፤ በዚ​ያም በቈ​ረ​ጥ​ኸው በማ​ም​ለ​ኪያ ዐጸዱ እን​ጨት ላይ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት አቅ​ርብ” አለው።


እነ​ሆም፥ ሳኦል ከእ​ር​ሻው አር​ፍዶ መጣ፤ ሳኦ​ልም፥ “ሕዝቡ የሚ​ያ​ለ​ቅስ ምን ሆኖ ነው?” አለ። የኢ​ያ​ቢ​ስ​ንም ሰዎች ነገር ነገ​ሩት።


እር​ሱም፥ “ዘመ​ዶቼ በከ​ተማ ውስጥ መሥ​ዋ​ዕት አላ​ቸ​ውና፥ ወን​ድ​ሞቼም ጠር​ተ​ው​ኛ​ልና እባ​ክህ! አሰ​ና​ብ​ተኝ፤ አሁ​ንም በዐ​ይ​ኖ​ችህ ሞገስ አግ​ኝቼ እንደ ሆነ ልሂ​ድና ወን​ድ​ሞ​ቼን ልይ አለ፤ ስለ​ዚህ ወደ ንጉሥ ማዕድ አል​መ​ጣም” ብሎ መለ​ሰ​ለት።


የቤ​ት​ሳ​ሚስ ሰዎ​ችም በእ​ርሻ ውስጥ ስንዴ ያጭዱ ነበር፤ ዐይ​ና​ቸ​ው​ንም ከፍ አድ​ር​ገው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት አዩ፤ ደስ ብሎ​አ​ቸ​ውም ተቀ​በ​ሉ​አት።


የወ​ር​ቁም አይ​ጦች ቍጥር ለአ​ም​ስቱ የፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን አለ​ቆች እንደ ነበ​ሩት ከተ​ሞች ሁሉ ቍጥር እን​ዲሁ ነበረ፤ እነ​ር​ሱም እስከ ታላቁ ድን​ጋይ የሚ​ደ​ርሱ ቅጥር ያላ​ቸው ከተ​ሞ​ችና የፌ​ር​ዜ​ዎን መን​ደ​ሮች ናቸው። በዚ​ህም ድን​ጋይ ላይ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ታቦት አስ​ቀ​መጡ፤ ድን​ጋ​ዩም እስከ ዛሬ ድረስ በቤ​ት​ሳ​ሚ​ሳ​ዊው በኦ​ሴዕ እርሻ አለ።