ዘኍል 26:42 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም የዳን ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤ በስምዔ በኩል፣ የሰምዔያውያን ጐሣዎች። እነዚህ እንግዲህ የዳን ጐሣዎች ሲሆኑ፣ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በየወገናቸው የዳን ልጆች እነዚህ ናቸው፤ ከሰምዔ የሰምዔያውያን ወገን፤ በየወገናቸው የዳን ወገኖች እነዚህ ናቸው። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የዳን ነገድ ተወላጆች ሰሜዔና፤ ተወላጆቹ፥ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የብንያም ልጆች በየወገናቸው፤ ከበዓሌ የበዓላውያን ወገን፥ ከአሲቤር የአሲቤራውያን ወገን፥ ከአኪራን የአኪራናውያን ወገን፥ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በየወገናቸው የዳን ልጆች እነዚህ ናቸው፤ ከሰምዔ የሰምዔያውያን ወገን፤ በየወገናቸው የዳን ወገኖች እነዚህ ናቸው። |
ከዳን ዝርያ፦ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።