La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




መዝሙር 121:4 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

የእስራኤል ጠባቂ ከቶ አያንቀላፋም፤ ፈጽሞም አይተኛም።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

እነሆ፤ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም፤ አያንቀላፋምም።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እነሆ፥ የእስራኤል ጠባቂ አይተኛም አያንቀላፋምም።

Ver Capítulo

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

እንደ እርሷ ያሉት በአ​ን​ድ​ነት ከእ​ርሷ ጋር ናቸው። አቤቱ፥ ለስ​ምህ ይገዙ ዘንድ፥ ለእ​ስ​ራ​ኤል ምስ​ክር የሚ​ሆኑ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወገ​ኖች አሕ​ዛብ ወደ​ዚያ ይወ​ጣ​ሉና።

Ver Capítulo



መዝሙር 121:4
7 Referencias Cruzadas  

እኩለ ቀን ሲሆን ኤልያስ “ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ጸልዩ! እርሱ አምላክ አይደለም እንዴ እርሱ በሐሳብ ተውጦ ይሆናል! ወይም ራሱን ያዝናና ይሆናል! ወይም ወደ ሩቅ አገር ሄዶ ይሆናል! ወይም ተኝቶ ያንቀላፋ ይሆናልና እንዲነቃ ቀስቅሱት!” እያለ ያፌዝባቸው ጀመር፤


እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፥ የቤት ሠሪዎች ድካም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ የከተማ ጠባቂዎች ትጋት ከንቱ ነው።


እግዚአብሔር ብርሃኔና ደኅንነቴ ስለ ሆነ ማንንም አልፈራም እግዚአብሔር የሕይወቴ ከለላ ስለ ሆነ የሚያስፈራኝ ማነው?


ጥበበኛ ለመሆንና በዚህ ዓለም የሚደረገውንም ነገር ሁሉ መርምሬ ለማወቅ በሞከርኩ መጠን ሰው ሌት ከቀን ዕረፍት አጥቶ እንደሚኖር ተረዳሁ።


እኔ እግዚአብሔር እጠብቀዋለሁ በየጊዜውም ውሃ አጠጣዋለሁ፤ ማንም ሰው እንዳይጐዳው ሌሊትና ቀን እጠብቀዋለሁ።


ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት ሆነው ሌሊትና ቀን በመቅደሱ ያገለግሉታል፤ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውም መጠለያቸው ይሆናል።