ኢዮብ 17:2 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የሚሳለቁብኝ ከበቡኝ ዐይኔም የእነርሱን ጥላቻ ይመለከታል። አዲሱ መደበኛ ትርጒም አላጋጮች ከብበውኛል፤ ትኵረቴም ትንኰሳቸው ላይ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) አላጋጮች በእኔ ዘንድ አሉ፥ ዓይኔም ማስቈጣታቸውን ትመለከታለች። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) እየለመንሁ ደከምሁ፤ ምንስ አደርጋለሁ? ባዕዳንም ገንዘቤን ሰረቁኝ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) አላጋጮች በእኔ ዘንድ አሉ፥ ዓይኔም በማስቈጣታቸው አደረች። |
እግዚአብሔርን ጠርቼው የመለሰልኝ ጊዜ ነበር፤ አሁን እኔ የወዳጆቼ መሳቂያ ሆኛለሁ፤ ስሕተት የሌለብኝ ፍጹሙ እኔ የሰው ሁሉ መሳለቂያ ሆኛለሁ።