ኢያሱ 21:19 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የአሮን ልጆች የካህናት ከተሞች ሁሉ ከመሰማሪያቸው ጋር ዐሥራ ሦስት ከተሞች ናቸው። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ለካህናቱ ለአሮን ዝርያዎች ከነመሰማሪያቸው የተሰጧቸው ከተሞች ዐሥራ ሦስት ነበሩ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የአሮን ዘሮች ለሆኑት ካህናት ከግጦሽ ምድራቸው ጋር በድምሩ ዐሥራ ሦስት ከተሞች ተመደቡላቸው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የካህናቱ የአሮን ልጆች ከተሞች ከመሰማሪያዎቻቸው ጋር ዐሥራ ሦስት ናቸው፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የአሮን ልጆች የካህናት ከተሞች ከመሰምርያቸው ጋር አሥራ ሦስት ናቸው። |