ሕዝቅኤል 27:4 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ዳርቻሽ በባሕር ልብ ነው፤ ሠሪዎችሽ ውበትሽን ፍጹም አደረጉ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ዳርቻሽ በባሕር መካከል ነው፤ ሠሪዎችሽም ፍጹም ውብ አድርገውሻል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም መኖሪያሽ ባሕር ነው፤ ገንቢዎችሽ እንደ ተዋበች መርከብ ሠርተውሻል። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ዳርቻሽ በባሕር ውስጥ ነው፤ ልጆችሽም ውበትሽን ፈጽመዋል። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ዳርቻሽ በባሕር ውስጥ ነው፥ ሠሪዎችሽ ውበትሽን ፈጽመዋል። |
በባሕር መግቢያ ለምትኖረውና፥ በብዙ ደሴቶች ላይ ከሚኖሩ ሕዝቦች ጋር ለምትነግደው ጢሮስ እንዲህ በላት፦ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጢሮስ ሆይ፥ አንቺ፦ “በውበት ፍጹም ነኝ” ብለሻል።