La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ማሕልየ መሓልይ 5:11 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ራሱ ምዝምዝ ወርቅ ነው፥ ጸጉሩ የተዝረፈረፈ ነው፥ እንደ ቁራም ጥቁር ነው።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ራሱ የጠራ ወርቅ፣ ጠጕሩ ዞማ፣ እንደ ቍራም የጠቈረ ነው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

የእርሱ ራስ የወርቅ ሉል ይመስላል፤ ጠጒሩም ዞማና እንደ ቊራ የጠቆረ ነው።

Ver Capítulo

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ራሱ ምዝ​ምዝ ወርቅ ነው፤ ቈን​ዳ​ላው የተ​ዝ​ረ​ፈ​ረፈ ነው፥ እንደ ቍራ ጥቍ​ረ​ትም ጥቁር ነው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ራሱ ምዝምዝ ወርቅ ነው፥ ቈንዳላው የተዝረፈረፈ ነው፥ እንደ ቁራ ጥቁረትም ጥቁር ነው።

Ver Capítulo



ማሕልየ መሓልይ 5:11
8 Referencias Cruzadas  

ዐይኖቹ በውሃ ምንጮች አጠገብ እንዳሉ በወተት እንደ ታጠቡ በፈሳሽ ውኃ አጠገብ እንደ ተቀመጡ እንደ ርግቦች ናቸው።


እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል፥ የውዴ ድምፅ ነው፥ እርሱም ያንኳኳል፥ እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ የእኔ እንከን የለሽ፥ ራሴ በጠል፥ ጸጉሬም በሌሊት ነጠብጣብ ርሶአል።


ራስሽ እንደ ቀርሜሎስ ተራራ በላይሽ ነው፥ የራስሽም ጠጉር እንደ ሐምራዊ ሐር ነው፥ ንጉሡ በሹርባው ታስሮአል።


“የሰውም ጠጉር ከራሱ ቢመለጥ እርሱ ቡሀ ነው፤ ነገር ግን ንጹሕ ነው።


ራሱና የራሱ ጠጉርም እንደ ነጭ የበግ ጠጉር እንደ በረዶም ነጭ ነበሩ፤ ዐይኖቹም እንደ እሳት ነበልባል ነበሩ፤