Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


ኢዮብ 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ኢዮብ የተ​ወ​ለ​ደ​በ​ትን ቀን እንደ ረገመ

1 ከዚ​ያም በኋላ ኢዮብ አፉን ከፈተ፥ የተ​ወ​ለ​ደ​ባ​ት​ንም ቀን ረገመ።

2 እን​ዲ​ህም አለ፦

3 “ያች የተ​ወ​ለ​ድ​ሁ​ባት ቀን ትጥፋ፥ ያችም፦ ወንድ ልጅ ነው ያሉ​ባት ሌሊት።

4 ያች ቀን ጨለማ ትሁን፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከላይ አይ​መ​ል​ከ​ታት፥ ብር​ሃ​ንም አይ​ብ​ራ​ባት።

5 ጨለ​ማና የሞት ጥላ ያግ​ኙ​አት፤ ጭጋ​ግም ይም​ጣ​ባት፤

6 ያች ቀንም የተ​ረ​ገ​መች ትሁን። ያችም ሌሊት ጨለማ ይም​ጣ​ባት፤ በዓ​መቱ ቀኖች መካ​ከል አት​ኑር፤ በወ​ሮች ቀኖች ውስ​ጥም ገብታ አት​ቈ​ጠር።

7 ለዚ​ያም ሌሊት ጭንቅ ይሁን፥ እል​ልታ ወይም ደስታ አይ​ግ​ባ​ባት።

8 ነገር ግን ሌዋ​ታ​ንን ለመ​ግ​ደል የተ​ዘ​ጋጀ ያችን ቀን የሚ​ረ​ግም ይር​ገ​ማት።

9 የዚያ ሌሊት ኮከ​ቦች ይጨ​ልሙ፤ ሌሊ​ቱም በጨ​ለማ ይኑር፤ ወደ ብር​ሃ​ንም አይ​ምጣ፤ የን​ጋት ኮከ​ብም ሲወጣ አይይ፤

10 የእ​ና​ቴን ማኅ​ፀን ደጅ አል​ዘ​ጋ​ምና፥ መከ​ራ​ው​ንም ከዐ​ይኔ አል​ሰ​ወ​ረ​ምና።

11 በማ​ኅ​ፀን ሳለሁ ስለ ምን አል​ሞ​ት​ሁም? ከሆ​ድስ በወ​ጣሁ ጊዜ ወዲ​ያ​ውኑ ስለ ምን አል​ጠ​ፋ​ሁም?

12 ጕል​በ​ቶች ስለ ምን ደገ​ፉኝ? ጡትስ ስለ ምን ጠባሁ?

13 አሁ​ንም ተኝቼ ዝም ባልሁ ነበር፤ አን​ቀ​ላ​ፍ​ቼም ባረ​ፍሁ ነበር፤

14 በሰ​ይ​ፋ​ቸው ከከ​በሩ ከም​ድር ነገ​ሥ​ታ​ትና መካ​ሮች ጋር፥

15 ወይም ወር​ቅን ካበዙ፥ ቤታ​ቸ​ው​ንም ብር ከሞሉ አለ​ቆች ጋር፥

16 ወይም ከእ​ናቱ ማኅ​ፀን እንደ ወጣ ጭን​ጋፍ፥ ብር​ሃ​ንም እን​ዳ​ላዩ ሕፃ​ናት በሆ​ንሁ ነበር።

17 ኃጥ​ኣን በዚያ በቍ​ጣው መቅ​ሠ​ፍት ይቃ​ጠ​ላሉ፤ በዚ​ያም በሥ​ጋ​ቸው የተ​ጨ​ነ​ቁት ያር​ፋሉ።

18 በዚ​ያም የጥ​ንት ዘመን ሰዎች በአ​ን​ድ​ነት፥ የአ​ስ​ጨ​ና​ቂ​ውን ድምፅ አይ​ሰ​ሙም።

19 ታና​ሹና ታላቁ በዚያ አሉ፤ ጌታ​ውን ያገ​ለ​ገለ ባሪ​ያም በዚያ አለ።

20 በመ​ራ​ራ​ነት ላሉት ብር​ሃን፥ በነ​ፍስ ለተ​ጨ​ነ​ቁ​ትም ሕይ​ወት፥

21 የተ​ሰ​ወረ ሀብ​ትን ከሚ​ቈ​ፍሩ ይልቅ፥ ሞትን ለሚ​መኙ ለማ​ያ​ገ​ኙ​ትም፥

22 ባገ​ኙ​ትም ጊዜ ደስ ለሚ​ላ​ቸው፥ ሕይ​ወት ስለ ምን ተሰጠ?

23 ሞት ለሰው ዕረ​ፍቱ ነው፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከእ​ርሱ ከለ​ከ​ለው።

24 ከአ​ዝ​መ​ራዬ በፊት ልቅ​ሶዬ መጥ​ቶ​አ​ልና፥ ስለ ደረ​ሰ​ብ​ኝም አስ​ፈሪ ነገር ሁል​ጊዜ አለ​ቅ​ሳ​ለሁ።

25 የተ​ጠ​ራ​ጠ​ር​ሁት ነገር መጥ​ቶ​ብ​ኛ​ልና፥ ያሰ​ብ​ሁ​ትም ደር​ሶ​ብ​ኛል።

26 ተዘ​ልዬ አል​ተ​ቀ​መ​ጥ​ሁም፥ ፀጥ​ታም አላ​ገ​ኘ​ሁም፥ አላ​ረ​ፍ​ሁም። ነገር ግን መከራ ደረ​ሰ​ች​ብኝ።”

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos