ክፉ ሰው ከጻድቅ ጋር በተቀላቀለ ጊዜ ይከፋል፥ የሰላም ድምፅንም ይጠላል።
ለማይታወቅ ሰው ዋስ የሚሆን መከራ ያገኘዋል፤ ዋስትና ለመስጠት እጅ የማይመታ ግን ምንም አይደርስበትም።
ለእንግዳ ሰው የሚዋስ ክፉ መከራን ይቀበላል፥ ዋስ መሆንን የሚጠላ ግን ይድናል።
የማታውቀውን ሰው ዕዳ ለመክፈል ዋስ ብትሆን፥ በችግር ላይ ትወድቃለህ፤ ዋስ መሆን ቢቀርብህ ግን የተሻለ ነው።
አላዋቂ ሰው አጋና ይመታል፥ ለባልንጀራውም ዋስ እንደሚሆን በራሱ ደስ ይለዋል።
ለማያውቀው ከተዋሰ ሰው ልብሱን ውሰድ፥ ለእንግዳ የተዋሰውንም እርሱን አግተው።