La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዮሐንስ 3:31 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ከላይ የመ​ጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከም​ድር የተ​ገ​ኘ​ውም ምድ​ራዊ ነው፤ የም​ድ​ሩ​ንም ይና​ገ​ራል፤ ከሰ​ማይ የመ​ጣው ግን ከሁሉ በላይ ነው።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

“ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሆነው የምድር ነው፤ የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው፥ የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሆነ ምድራዊ ነው፤ የምድርንም ነገር ይናገራል፤ ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው።

Ver Capítulo



ዮሐንስ 3:31
22 Referencias Cruzadas  

ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ።


ምስ​ክሩ ዮሐ​ንስ ስለ እርሱ ድም​ፁን ከፍ አድ​ርጎ ተና​ገረ፤ እን​ዲ​ህም አለ፥ “እኔ ስለ እርሱ ከእኔ በፊት የነ​በረ ከእኔ በኋላ ይመ​ጣል ያል​ኋ​ችሁ ሰው ይህ ነው፥ እርሱ ከእኔ አስ​ቀ​ድሞ ነበ​ረና።”


ከእኔ በኋላ የሚ​መ​ጣው፥ ከእኔ በፊት የነ​በ​ረው፥ የጫ​ማ​ውን ጠፍር ልፈታ እንኳ የማ​ይ​ገ​ባኝ ነው።”


ከእኔ በፊት የነ​በረ ሰው ከእኔ በኋላ ይመ​ጣል ብዬ ስለ እርሱ የነ​ገ​ር​ኋ​ችሁ ይህ ነው፤ እርሱ ከእኔ አስ​ቀ​ድሞ ነበ​ርና።


የእ​ርሱ ትበ​ዛ​ለች፤ የእኔ ግን ታንስ ዘንድ ይገ​ባል።”


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ጀራ ከሰ​ማይ የሚ​ወ​ርድ፤ ለዓ​ለ​ምም ሕይ​ወ​ትን የሚ​ሰጥ ነውና።”


“ከሰ​ማይ የወ​ረደ የሕ​ይ​ወት እን​ጀራ እኔ ነኝ፤ ከዚህ እን​ጀራ የሚ​በላ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል፤ ስለ ዓለም ሕይ​ወት የም​ሰ​ጠው ይህ እን​ጀራ ሥጋዬ ነው።”


እር​ሱም እን​ዲህ አላ​ቸው፥ “እና​ን​ተስ ከታች ናችሁ፤ እኔ ግን ከላይ ነኝ፤ እና​ንተ ከዚህ ዓለም ናችሁ፤ እኔ ግን ከዚህ ዓለም አይ​ደ​ለ​ሁም።


ቃሉን ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ላከ፤ በኢ​የ​ሱስ ክር​ስ​ቶ​ስም ሰላ​ምን ነገ​ራ​ቸው፤ እር​ሱም የሁሉ ገዢ ነው።


እነ​ር​ሱም አባ​ቶ​ቻ​ችን ናቸው፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ክር​ስ​ቶስ በሥጋ ተወ​ለደ፤ እር​ሱም ከሁሉ በላይ የሆነ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ቡሩክ አም​ላክ ነው፤ አሜን።


ፊተ​ኛ​ይ​ቱም ደግሞ የአ​ገ​ል​ግ​ሎት ሥር​ዐ​ትና የዚህ ዓለም የሆ​ነው መቅ​ደስ ነበ​ራት።


እርሱም መላእክትና ሥልጣናት ኀይላትም ከተገዙለት በኋላ ወደ ሰማይ ሄዶ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ።


እነርሱ ከዓለም ናቸው፤ ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ ዓለሙም ይሰማቸዋል።


በልብሱና በጭኑም የተጻፈበት “የነገሥታት ንጉሥና የጌታዎች ጌታ” የሚል ስም አለው።