La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘፍጥረት 21:7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ደግ​ሞም ሣራ “በእ​ር​ጅ​ናዋ የወ​ለ​ደ​ች​ውን ሕፃን እን​ድ​ታ​ጠባ ለአ​ብ​ር​ሃም ማን በነ​ገ​ረው?” አለች።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ደግሞም፣ “ለመሆኑ፣ ‘ሣራ ልጆች ታጠባለች’ ብሎ ለአብርሃም ማን ተናግሮት ያውቅ ነበር? ይኸው በስተርጅናው ወንድ ልጅ ወለድሁለት” አለች።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ደግሞም፦ “ሣራ ልጆችን እንድታጠባ ለአብርሃም ማን በነገረው? በእርጅናው ልጅን ወልጄለታለሁና” አለች።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ቀጥላም “ ‘ሣራ ለአብርሃም ልጅ ወልዳ ታጠባለች’ ብሎ የሚናገር ከቶ ማን ነበር? አሁን ግን እነሆ በእርጅናው ዘመን ወንድ ልጅ ወለድኩለት” አለች።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ደግሞም፥ ሣራ ልጆችን እንድታጠባ ለአብርሃም ማን በነገረው? በእርጅናው ልጅን ወልጄለታለሁና አለች።

Ver Capítulo



ዘፍጥረት 21:7
15 Referencias Cruzadas  

አብ​ር​ሃ​ምም በግ​ን​ባሩ ወደቀ፤ ሳቀም፤ በል​ቡም እን​ዲህ ብሎ አሰበ፥ “የመቶ ዓመት ሰው ስሆን በውኑ እኔ ልጅ እወ​ል​ዳ​ለ​ሁን? ዘጠና ዓመት የሆ​ና​ትም ሣራ ትወ​ል​ዳ​ለ​ችን?”


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አብ​ር​ሃ​ምን አለው፥ “ሣራን ለብ​ቻዋ በል​ብዋ ምን አሳ​ቃት? እስከ ዛሬ ገና ነኝን? በእ​ው​ነ​ትስ እወ​ል​ዳ​ለ​ሁን? ጌታ​ዬም አር​ጅ​ት​ዋል እነሆ፥ እኔም አር​ጅ​ቻ​ለሁ ብላ​ለ​ችና።


ሕፃ​ኑም አደገ፤ ጡት​ንም አስ​ጣ​ሉት፤ አብ​ር​ሃ​ምም ይስ​ሐ​ቅን ጡት ባስ​ጣ​ለ​በት ቀን ትልቅ ግብ​ዣን አደ​ረገ።


የቴ​ቄ​ም​ናስ እኅት ወንድ ልጅ ጌን​ባ​ትን ለአ​ዴር ወለ​ደ​ች​ለት፤ ቴቄ​ም​ና​ስም በፈ​ር​ዖን ልጆች መካ​ከል አሳ​ደ​ገ​ችው፤ ጌን​ባ​ትም በፈ​ር​ዖን ልጆች መካ​ከል ነበረ።


ልጄ​ንም አጠባ ዘንድ በማ​ለዳ ብነሣ፥ ያን የሞ​ተ​ውን ልጅ አገ​ኘሁ፤ ነገር ግን ብር​ሃን በሆነ ጊዜ ተመ​ለ​ከ​ት​ሁት፤ እነ​ሆም፥ የወ​ለ​ድ​ሁት ልጄ አል​ነ​በ​ረም።”


አን​ቺም በል​ብሽ፦ የወ​ላድ መካን ሆኛ​ለ​ሁና፥ እኔም መበ​ለት ነኝና እነ​ዚ​ህን ማን ወለ​ደ​ልኝ? እነ​ዚ​ህ​ንስ ማን አሳ​ደ​ጋ​ቸው? እነሆ፥ ብቻ​ዬን ቀርቼ ነበር፤ እነ​ዚ​ህስ ከወ​ዴት መጡ?” ትያ​ለሽ።


ከቶ እን​ዲህ ያለ ነገ​ርን ማን ሰም​ቶ​አል? እን​ዲ​ህስ ያለ ነገ​ርን ማን አይ​ቶ​አል? በውኑ ሀገር በአ​ንድ ቀን ታም​ጣ​ለ​ችን? ወይስ በአ​ንድ ጊዜ ሕዝብ ይወ​ለ​ዳ​ልን? ጽዮን እን​ዳ​ማ​ጠች ወዲ​ያው ልጆ​ች​ዋን ወል​ዳ​ለ​ችና።


ወንድ ልጅ ተወ​ል​ዶ​ል​ሃል ብሎ ለአ​ባቴ የም​ሥ​ራች ነግሮ ደስ ያሰ​ኘው ሰው የተ​ረ​ገመ ይሁን።


በያ​ዕ​ቆብ ላይ ጥን​ቆላ የለም፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ላይ ምዋ​ርት የለም፤ በየ​ጊ​ዜው ስለ ያዕ​ቆ​ብና ስለ እስ​ራ​ኤል፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምን አደ​ረገ? ይባ​ላል።


ብዙ ልዩ ልዩ የሆ​ነች የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጥበብ አሁን በቤተ ክር​ስ​ቲ​ያን በኩል በሰ​ማ​ያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት አለ​ቆ​ችና ሥል​ጣ​ናት ትታ​ወቅ ዘንድ፤