La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




መክብብ 8:8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

መን​ፈ​ስን ለማ​ስ​ቀ​ረት በመ​ን​ፈሱ ላይ ሥል​ጣን ያለው ሰው የለም፤ በሞ​ትም ቀን ሥል​ጣን የለ​ውም፤ በጦ​ር​ነ​ትም ጊዜ ስን​ብት የለም፥ ኀጢ​አ​ትም ሠሪ​ውን አያ​ድ​ነ​ውም።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሰው ነፋስን መቈጣጠር አይችልም፤ በዕለተ ሞቱም ላይ ሥልጣን ያለው ማንም የለም፤ በጦርነት ጊዜ ማንም ከግዴታ ነጻ እንደማይሆን፣ ክፋትም የሚለማመዷትን አትለቃቸውም።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

መንፈስን ለማገድ በመንፈስ ላይ ሥልጣን ያለው ሰው የለም፥ በሞቱም ቀን ላይ ሥልጣን የለውም፥ በጦርነትም ውስጥ መሰናበቻ የለም፥ ክፋትም ሠሪውን አያድነውም።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

የሕይወትን እስትንፋስ ለማስቀረትና የሞትን ቀን ለመለወጥ የሚችል ማንም የለም፤ ማንም ሰው ከጦር ሜዳ መሰናበት እንደማይችል ክፋትም ክፉ ሠሪዎችን አይለቃቸውም።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

መንፈስን ለማስቀረት በመንፈስ ላይ ሥልጣን ያለው ሰው የለም፥ በሞቱም ቀን ሥልጣን የለውም፥ በሰልፍም ስንብቻ የለም፥ ኃጢአትም ሠሪውን አያድነውም።

Ver Capítulo



መክብብ 8:8
21 Referencias Cruzadas  

ሞትን እን​ሞ​ታ​ለ​ንና፥ በም​ድ​ርም ላይ እንደ ፈሰ​ሰና እን​ደ​ማ​ይ​መ​ለስ ውኃ እን​ሆ​ና​ለ​ንና፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ነፍ​ስን ይወ​ስ​ዳል። የተ​ጣ​ለ​ው​ንም ከእ​ርሱ ያርቅ ዘንድ ያስ​ባል።


በኋ​ላ​ቸ​ውም እስከ ዮር​ዳ​ኖስ ድረስ ተከ​ት​ለ​ዋ​ቸው ሄዱ፤ እነ​ሆም፥ ሶር​ያ​ው​ያን ሲሸሹ የጣ​ሉት ልብ​ስና ዕቃ መን​ገ​ዱን ሁሉ ሞልቶ አገኙ። እነ​ዚያ መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችም ተመ​ል​ሰው ለእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ ነገ​ሩት።


በም​ድር ላይ አንድ ቀንም እንኳ ቢኖር፤ ወሮ​ቹም በአ​ንተ ዘንድ የተ​ቈ​ጠሩ ናቸው፤ ዘመ​ኑ​ንም ወስ​ነህ ትሰ​ጠ​ዋ​ለህ፤ እር​ሱም ከዚያ አያ​ል​ፍም።


በእ​ርሱ ያለ መን​ፈ​ሱን፥ ሊያ​ጸ​ናና ሊይዝ ቢወ​ድድ፥


ኀጢ​አ​ተ​ኞች ወደ ሲኦል ይመ​ለሱ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ረሱ አሕ​ዛ​ብም ሁሉ።


ከዐመፃ የማይርቅ ሰው ይጠፋል፤ የጻድቃን ሥር ግን አይነቀልም።


ኃጥእ በክፋቱ ይወገዳል፤ በቸርነቱ የሚታመን ግን ጻድቅ ነው።


የሰው ልጆች ነፍስ ወደ ላይ እን​ደ​ም​ት​ወጣ፥ የእ​ን​ስ​ሳም ነፍስ ወደ ታች ወደ ምድር እን​ደ​ም​ት​ወ​ርድ የሚ​ያ​ውቅ ማን ነው?


ለኃ​ጥእ ግን ደኅ​ን​ነት የለ​ውም፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት አይ​ፈ​ራ​ምና ዘመኑ እንደ ጥላ አት​ረ​ዝ​ምም።


ሰውም ጊዜ​ውን አያ​ው​ቅም፤ በክፉ መረብ እንደ ተጠ​መዱ ዓሣ​ዎች ፥ በወ​ጥ​መ​ድም እንደ ተያዙ ወፎች፥ እን​ዲሁ የሰው ልጆች በክፉ ጊዜ በድ​ን​ገት ሲወ​ድ​ቅ​ባ​ቸው ይጠ​መ​ዳሉ።


እና​ን​ተም “ከሲ​ኦል ጋር ተማ​ም​ለ​ናል፤ ከሞ​ትም ጋር ቃል ኪዳን አድ​ር​ገ​ናል፤ ሐሰ​ት​ንም መሸ​ሸ​ጊ​ያን አድ​ር​ገ​ና​ልና፥ በሐ​ሰ​ትም ተሰ​ው​ረ​ና​ልና፥ ዐውሎ ነፋ​ስም ባለፈ ጊዜ አይ​ደ​ር​ስ​ብ​ንም” ትላ​ላ​ች​ሁና፥


ከሞ​ትም ጋር ያደ​ረ​ጋ​ች​ሁት ቃል ኪዳን ይፈ​ር​ሳል፤ ከኢ​ኦ​ልም ጋር የተ​ማ​ማ​ላ​ች​ሁት መሐላ አይ​ጸ​ናም፤ የሚ​ያ​ልፍ ዐውሎ ነፋስ በመጣ ጊዜ ይረ​ግ​ጣ​ች​ኋል፤ ትደ​ክ​ማ​ላ​ች​ሁም።


በክ​ፋ​ትሽ ታም​ነ​ሻል፤ አንቺ ግን፥ “እኔ ነኝ፤ ከእኔ በቀር ሌላ የለም” ብለ​ሻል፤ በዝ​ሙ​ትሽ ኀፍ​ረት ያሰ​ብ​ሽ​ው​ንም ዕወቂ፤ በል​ብሽ፥ “እኔ ነኝ ከእ​ኔም በቀር ሌላ የለም” ብለ​ሻ​ልና።


በው​ር​ደት ይዘ​ራል፤ በክ​ብር ይነ​ሣል፤ በድ​ካም ይዘ​ራል፤ በኀ​ይል ይነ​ሣል።


በድ​ካም ተሰ​ቅ​ሎ​አ​ልና፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኀይል ሕያው ነውና፤ እኛም ከእ​ርሱ ጋር እን​ደ​ክ​ማ​ለ​ንና፤ ነገር ግን ስለ እና​ንተ በሚ​ሆን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀይል ከእ​ርሱ ጋር በሕ​ይ​ወት እን​ኖ​ራ​ለን።


ለሰው አንድ ጊዜ ሞት፥ ከዚ​ያም በኋላ ፍርድ እን​ደ​ሚ​ጠ​ብ​ቀው፥