La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ሳሙኤል 20:11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ከኢ​ዮ​አ​ብም ብላ​ቴ​ኖች አንዱ በአ​ሜ​ሳይ ሬሳ አጠ​ገብ ቆሞ፥ “ኢዮ​አብ የሚ​ፈ​ል​ገው ምን​ድን ነው? የዳ​ዊ​ትም የሆኑ ኢዮ​አ​ብን የሚ​ከ​ተሉ እነ​ማን ናቸው?” አለ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

በአሜሳይ ሬሳ አጠገብ ከቆሙት ከኢዮአብ ሰዎች አንዱ፤ “ኢዮአብን የሚወድድ፣ የዳዊትም የሆነ ሁሉ ኢዮአብን ይከተል!” አለ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

በአማሳይ ሬሳ አጠገብ ከቆሙት ከኢዮአብ ሰዎች አንዱ፤ “ኢዮአብን የሚወድ፥ የዳዊትም የሆነ ሁሉ ኢዮአብን ይከተል!” አለ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ከኢዮአብ ወታደሮች አንዱ በዐማሳ ሬሳ አጠገብ ቆሞ “ኢዮአብንና ዳዊትን የምትከተሉ ሁሉ ኢዮአብን ተከተሉ!” ሲል ድምፁን ከፍ አድርጎ ተናገረ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ኢዮአብና ወንድሙ አቢሳ የቢክሪን ልጅ ሳቤዔን አሳደዱ። ከኢዮአብም ብላቴኖች አንዱ በአሜሳይ ሬሳ አጠገብ ቆሞ፦ ለኢዮአብ ወዳጅ የሚሆን ለዳዊትም የሆነ ሁሉ ኢዮአብን ይከተል ይል ነበር።

Ver Capítulo



2 ሳሙኤል 20:11
6 Referencias Cruzadas  

አሜ​ሳ​ይም በደም ተነ​ክሮ በመ​ን​ገድ መካ​ከል ወድቆ ነበር፤ ያም ሰው ወደ እርሱ የሚ​መጣ ሁሉ ሲቆም አይ​ቶ​አ​ልና ሕዝቡ ሁሉ እንደ ቆመ ባየ ጊዜ አሜ​ሳ​ይን ከመ​ን​ገድ ላይ ወደ እርሻ ውስጥ ፈቀቅ አደ​ረ​ገው፤ በል​ብ​ስም ከደ​ነው።


ከመ​ን​ገ​ድም ፈጥኖ ራቅ ባለ ጊዜ የእ​ስ​ራ​ኤል ሰው ሁሉ የቢ​ኮ​ሪን ልጅ ሳቡ​ሄን ለማ​ሳ​ደድ ኢዮ​አ​ብን ተከ​ትሎ ያልፍ ነበር።


ነገሩ እን​ዲህ አይ​ደ​ለም፤ ከተ​ራ​ራ​ማው ከኤ​ፍ​ሬም ሀገር የሚ​ሆን የቢ​ኮሪ ልጅ ሳቡሄ የሚ​ባል አንድ ሰው ግን በን​ጉሡ በዳ​ዊት ላይ እጁን አነሣ፤ እር​ሱን ብቻ​ውን ስጡኝ፤ እኔም ከከ​ተ​ማ​ዪቱ እር​ቃ​ለሁ” አላት። ሴቲ​ቱም ኢዮ​አ​ብን፥ “እነሆ፥ ራሱ ከቅ​ጥር ላይ ይጣ​ል​ል​ሃል” አለ​ችው።


ንጉ​ሡም አሜ​ሳ​ይን፥ “የይ​ሁ​ዳን ሰዎች ሁሉ በሦ​ስት ቀን ውስጥ ጥራ​ልኝ፤ አን​ተም አብ​ረህ በዚህ ሁን” አለው።


ፊቱ​ንም አቅ​ንቶ በመ​ስ​ኮቱ አያት። “አንቺ ማን ነሽ? ወደ​ዚህ ወደ እኔ ውረጂ” አላት። ከዚ​ህም በኋላ ሁለት ጃን​ደ​ረ​ቦች ወደ እርሱ ተመ​ለ​ከቱ።