ኢያሱ 21:20 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም የሌዊ ልጅ የቀዓት ጐሣዎች ለሆኑት ለሌሎቹ ደግሞ ከኤፍሬም ነገድ ላይ ተከፍለው የሚከተሉት ከተሞች በዕጣ ተመደቡላቸው። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ለቀሩትም ለቀዓት ልጆች የሌዋውያን ለሆኑ የቀዓት ወገኖች የዕጣቸው ከተሞች ከኤፍሬም ነገድ ደረሱአቸው። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ለቀሩት ከሌዊ ነገድ ለሆኑት የቀዓት ጐሣዎች ከኤፍሬም ነገድ ይዞታ ተከፍሎ ተሰጣቸው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ለቀሩትም ለሌዋውያኑ ለቀዓት ልጆች የዕጣቸው ከተሞች ከኤፍሬም ነገድ ደረሱአቸው። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ለቀሩትም ለቀዓት ልጆች ወገኖች ሌዋውያን የዕጣቸው ከተሞች ከኤፍሬም ነገድ ደረሱአቸው። |