2 ነገሥት 10:28 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም በዚህ ሁኔታም ኢዩ የበኣልን አምልኮ ከእስራኤል አስወገደ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ኢዩ በእስራኤል የነበረውን የበዓልን ጣዖታዊ አምልኮ ያስወገደው በዚህ ዓይነት ዘዴ ነበር፤ አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ኢዩ በእስራኤል የነበረውን የባዓልን ጣዖታዊ አምልኮ ያስወገደው በዚህ ዐይነት ዘዴ ነበር፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) እንዲሁም ኢዩ በዓልን ከእስራኤል አጠፋ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) እንዲሁም ኢዩ በኣልን ከእስራኤል አጠፋ። |
ለበኣል አማልክት ዕጣን ስላጠነችባቸው ቀናት እቀጣታለሁ፤ በጌጣጌጥና በቀለበቶች ራሷን አስጊጣለች፤ ውሽሞቿንም ተከትላ ሄዳለች፤ እኔን ግን ረስታለች” ይላል እግዚአብሔር።