ዮናስ 4:1 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ዮናስ በዚህ ነገር ስላልተደሰተ ተበሳጨ፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም ዮናስ ግን ፈጽሞ አልተደሰተም፤ ስለዚህም ተቈጣ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ይህም ዮናስን ከቶ ደስ አላሰኘውም፥ ክፉኛም አበሳጨው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ዮናስም ፈጽሞ አዘነ፤ ተከዘም። |
እግዚአብሔርም “ስለዚህች ቅል ልትበሳጭ ይገባሃልን?” አለው። ዮናስም “በእርግጥ መበሳጨት ይገባኛል፤ እንዲያውም በንዴት እስከምሞት ድረስ መበሳጨት አለብኝ!” አለ።
ምሳ የጋበዘው ፈሪሳዊ ይህን ባየ ጊዜ፥ “ይህ ሰው ነቢይ ቢሆን ኖሮ ይህች የምትዳስሰው ሴት ማን እንደ ሆነችና ምን ዐይነት ኃጢአተኛ እንደ ሆነች ባወቀ ነበር፤” ሲል በልቡ አሰበ።
ጳውሎስና በርናባስ ግን እንዲህ ሲሉ በድፍረት ተናገሩ፤ “የእግዚአብሔር ቃል አስቀድሞ ለእናንተ እንዲነገር አስፈላጊ ነው፤ እናንተ አንቀበልም ካላችሁና የዘለዓለም ሕይወት እንደማይገባችሁ በራሳችሁ ከፈረዳችሁ ግን እነሆ፥ እኛ ዞር ብለን ወደ አሕዛብ እንሄዳለን።