መክብብ 7:19 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም በአንዲት ከተማ ከሚኖሩ ከዐሥር ገዥዎች ይበልጥ ጥበብ ለአስተዋይ ሰው ብርታትን ትሰጠዋለች። አዲሱ መደበኛ ትርጒም በአንድ ከተማ ካሉ ዐሥር ገዦች ይልቅ፣ ጥበብ ጠቢቡን ሰው ኀያል ታደርገዋለች። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በከተማ ከሚኖሩ ከዐሥር ገዢዎች ይልቅ ጥበብ ጠቢብን ታበረታለች። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በከተማ ከሚኖሩ ዐሥር ገዢዎች ይልቅ ጥበብ ጠቢብን ትረዳዋለች። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በከተማ ከሚኖሩ ከአሥር ገዢዎች ይልቅ ጥበብ ጠቢብን ታበረታለች። |