ሮሜ 6:7 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የሞተስ ከኃጢአት ነጻ ወጥቶአልና። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ምክንያቱም የሞተ ከኀጢአት ነጻ ወጥቷል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የሞተ ሰው ለኃጢአት ከመገዛት ነጻ ነው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የሞተስ ከኀጢአት ነጻ ወጥቶአል። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ነገር ግን ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር እናምናለን፤ |
ስለዚህ ወንድሞቼ ሆይ! እናንተ ደግሞ በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ተገድላችኋል፤ እናንተ ለሌላው፥ ከሙታን ለተነሣው፥ ለእርሱ እንድትሆኑና ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ ነው።
እንግዲህ ክርስቶስ በሥጋ ስለ እኛ መከራን በመቀበሉ፥ እናንተም በዚህ ሐሳብ ራሳችሁን አስታጥቁ፤ ምክንያቱም በሥጋ መከራን የተቀበለ ኃጢአትን ትቶአል።