ዐይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና፤
ዐይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን፣
ማዳንህን በዐይኔ አይቻለሁ፤
ዐይኖች ትድግናህን አይተዋልና።
ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤
ጌታ ሆይ፥ መድኃኒትህን እጠብቃለሁ።
አቤቱ፥ ማዳንህን ተስፋ አደርግሁ፥ ትእዛዛትህንም ጠበቅሁ።
አቤቱ፥ ማዳንህን ናፈቅሁ፥ ሕግህም ተድላዬ ነው።
እርሱም፦ “የያዕቆብን ነገዶች እንድታስነሣ ከእስራኤልም የተረፉትን እንድትመልስ አገልጋዬ እንድትሆን እጅግ ቀላል ነገር ነውና ማዳኔ እስከ ምድር ዳር እንዲደርስ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌ ሰጥቼሃለሁ ይላል።
ጌታ የተቀደሰውን ክንዱን በአሕዛብ ሁሉ ፊት ገልጦአል፥ በምድር ዳርቻ የሚኖሩትም ሁሉ የአምላካችንን መድኃኒት ያያሉ።
እርሱም በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸው ነው፤
ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ፤”
ሲል መልካም ተናገረ። እንግዲህ ይህ የእግዚአብሔር ማዳን ለአሕዛብ እንደ ተላከ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፤ እነርሱ ደግሞ ይሰሙታል።