የፋሲካውንም መሥዋዕት እንደ ሥርዓቱ በእሳት ጠበሱ፤ የተቀደሰውንም ቁርባን በምንቸትና በሰታቴ በድስትም ቀቀሉ፥ ለሕዝቡም ሁሉ በፍጥነት አደረሱ።
ዘሌዋውያን 6:28 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የሚቀቀልበትም ሸክላ ይሰበራል፤ ነገር ግን በናስ ዕቃ የተቀቀለ እንደሆነ ይፈገፈጋል፥ በውኃም ይለቀለቃል። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ሥጋው የተቀቀለበት የሸክላ ዕቃ ይሰበር፤ የናስ ዕቃ ከሆነ ግን ተፈግፍጎ በውሃ ይታጠብ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሥጋ የተቀቀለበት ማናቸውም የሸክላ ዕቃ ይሰበር፤ ሥጋው የተቀቀለው በነሐስ ዕቃ ከሆነም ተፈግፍጎ በውሃ ይለቃለቅ። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የሚቀቀልበትን ሸክላ ይሰብሩታል፤ በናስም ዕቃ ቢቀቀል ይፈገፍጉታል፤ በውኃም ያጥቡታል። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የሚቀቀልበትም ሸክላ ይሰበራል፤ በናስም ዕቃ ቢቀቀል ይፈገፈጋል፥ በውኃም ይለቀለቃል። |
የፋሲካውንም መሥዋዕት እንደ ሥርዓቱ በእሳት ጠበሱ፤ የተቀደሰውንም ቁርባን በምንቸትና በሰታቴ በድስትም ቀቀሉ፥ ለሕዝቡም ሁሉ በፍጥነት አደረሱ።