ዕብራውያን 2:5 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ስለ እርሱ የምንናገርለት፥ የሚመጣውን ዓለም ያስገዛው ለመላእክት አይደለምና። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ይህን የምንናገርለትን መጪውን ዓለም ለመላእክት አላስገዛም። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም እግዚአብሔር ወደ ፊት የሚመጣውን፥ ይህን የምንነጋገርበትን ዓለም ለመላእክት አላስገዛም የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ስለ እርሱ የምንናገርለትን የሚመጣውን ዓለም ለመላእክት ያስገዛ አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ስለ እርሱ የምንናገርበትን የሚመጣውን ዓለም ለመላእክት ያስገዛው አይደለምና። |
ሰባተኛው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ በሰማይም እንዲህ የሚሉ ታላላቅ ድምፆች ተሰሙ፦ “የዓለም መንግሥት የጌታችንና የመሢሑ ሆነች፤ ለዘለዓለምም እስከ ዘለዓለም ይነግሣል፤”