ዕዝራ 8:24 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ከካህናቱ መሪዎች ዐሥራ ሁለት ሰዎችን፥ ሼሬብያን፥ ሐሻብያንና ከእነርሱም ጋር ዐሥር ወንድሞቻቸውን ለየሁ፤ አዲሱ መደበኛ ትርጒም እኔም ከካህናት አለቆች ዐሥራ ሁለት ሰዎችን፣ ከእነርሱም ጋራ ሰራብያን፣ ሐሸቢያንና ከወንድሞቻቸውም መካከል ዐሥር ሰዎችን ለየሁ፤ አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም መሪዎች ከሆኑት ካህናት መካከል ሼሬብያን፥ ሐሻብያንና ሌሎችንም ዐሥር ሰዎች መረጥሁ፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ከካህናቱም አለቆች ዐሥራ ሁለት ሰዎችን፥ ሰራብያንና ሐሳብያን፥ ከእነርሱም ጋር ዐሥር ወንድሞቻቸውን ለየሁ፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ከካህናቱም አለቆች አሥራ ሁለት ሰዎችን፥ ሰራብያንና ሐሸቢያን ከእነርሱም ጋር አሥር ወንድሞቻቸውን ለየሁ፤ |