La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ሕዝቅኤል 8:8 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እርሱም እንዲህ አለኝ፦ የሰው ልጅ ሆይ ግንቡን ቦርቡረው አለኝ፥ ግንቡንም በቦረቦርሁት ጊዜ እነሆ አንድ መግቢያ አገኘሁ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

እርሱም፣ “የሰው ልጅ ሆይ፤ ግንቡን ንደለው” አለኝ፤ እኔም ግንቡን ነደልሁት፤ አንድ በርም አገኘሁ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

“የሰው ልጅ ሆይ! በዚህ በኩል ግንቡን ሸንቊረው” አለኝ፤ በሸነቈርኩትም ጊዜ አንድ በር አገኘሁ፤

Ver Capítulo

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

እር​ሱም፥ “የሰው ልጅ ሆይ! ግን​ቡን ንደ​ለው” አለኝ፤ ግን​ቡ​ንም በነ​ደ​ል​ሁት ጊዜ ደጃፍ አገ​ኘሁ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

እርሱም፦ የሰው ልጅ ሆይ፥ ግንቡን ንደለው አለኝ፥ ግንቡንም በነደልሁት ጊዜ መዝጊያ አገኘሁ።

Ver Capítulo



ሕዝቅኤል 8:8
7 Referencias Cruzadas  

ክፋትን የሚሠሩ የሚደበቁበት ጨለማ ወይም የሞት ጥላ የለም።


ምክራቸውን ጥልቅ አድርገው ከጌታ ለሚሰውሩ፥ ሥራቸውንም በጨለማ ውስጥ አድርገው፦ “ማን ያየናል? ወይስ ማን ያውቀናል?” ለሚሉ ወዮላቸው!


እንዲሁም ሲምሱ አልያዝሻቸውም ነገር ግን በልብሶችሽ ላይ የንጹሐን ድሆች ደም ተገኝቶአል፤ እነዚህን ሁሉ ነገሮች ብትፈጽሚም እንኳ


ሰው በስውር ቦታ ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ይላል ጌታ። ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል ጌታ።


ወደ አደባባዩ መግቢያም አመጣኝ፥ አየሁም፥ እነሆ በግንቡ ላይ ቀዳዳ ነበረ።


እርሱም እንዲህ አለኝ፦ ግባ፥ በዚህ የሚያደርጉትንም ክፉውን ርኩሰት ተመልከት።