ሕዝቅኤል 42:7 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በክፍሎቹ ትይዩ በውጭ ያለው ቅጥር፥ በክፍሎቹ ፊት ለፊት ያለው የውጭው አደባባይ ርዝመት አምሳ ክንድ ነበረ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ከክፍሎቹና፣ ከውጩ አደባባይ ትይዩ የሆነ የውጪ ግንብ አለ፤ ይህም በክፍሎቹ ፊት ለፊት ሆኖ ዐምሳ ክንድ ይረዝማል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከክፍሎቹ ፊት ለፊት ኀምሳ ክንድ ርዝመት ያለው በስተውጪው አደባባይ በኩል በክፍሎቹ ትይዩ አንድ ግንብ ነበር። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በውጭ በዕቃ ቤቶቹ አጠገብ ያለው፥ ወደ ውጭው አደባባይ የሚያመለክተው ቅጥር፥ በዕቃ ቤቶች ትይዩ የሆነ ርዝመቱ አምሳ ክንድ ነበረ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በውጭ በዕቃ ቤቶቹ አጠገብ ያለው፥ ወደ ውጭው አደባባይ የሚመለከተው ቅጥር፥ በዕቃ ቤቶች ትይዩ የሆነ፥ ርዝመቱ አምሳ ክንድ ነበረ። |