ዘፀአት 21:10 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ሌላይቱን ቢያገባ፥ ምግብዋን፥ ልብስዋንና የጋብቻ መብቷን አይቀንስባት። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ሌላ ሴት ቢያገባ፣ ለመጀመሪያ ሚስቱ ምግቧን፣ ልብሷንና የጋብቻ መብቷን አይከልክላት። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሁለተኛ ሚስት ቢያገባ ለመጀመሪያ ሚስቱ ምግብና ልብስ መስጠቱን አይተው፤ ቀድሞ የነበራትንም የጋብቻ መብት አይከልክላት። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ከእርስዋም ሌላ ቢያገባ፥ ቀለብዋን፥ ልብስዋንም፥ ለጋብቻዋም ተገቢውን ይስጣት፤ እንዳልበደላትም ምስክር ያሰማባት። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ከእርስዋ ሌላም ቢያጋባው፥ መኖዋን ልብስዋንም ለምንጣፍዋም ተገቢውን አያጕድልባት። |