ዘፀአት 16:36 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ዖሜርም የኢፍ አንድ አሥረኛ ነው። አዲሱ መደበኛ ትርጒም አንድ ጎሞር የኢፍ መስፈሪያ አንድ ዐሥረኛ ነው። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም በዚያን ጊዜ መደበኛ መስፈሪያዎች ኢፍና ጎሞር ይባሉ ነበሩ። ኢፍ ዐሥራ አምስት ኪሎ ሲመዝን ጎሞር አንድ ኪሎ ተኩል ነበር። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ወደ ፊኒቆንም ምድር እስኪመጡ ድረስ መና በሉ። ጎሞርም የሦስት ላዳን መስፈሪያ ዐሥረኛ ክፍል ነው። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ጎሞርም የኢፍ መስፈሪያ አሥረኛ ክፍል ነው። |
የኢፍና የባዶስ መስፈሪያ አንድ ይሁን፤ የባዶስ መስፈሪያ የቆሮስ መስፈሪያ አንድ አሥረኛ፥ የኢፍ መስፈሪያውም የቆሮስ መስፈሪያ አንድ አሥረኛ ይሁን። መለኪያው የቆሮስ መስፈሪያ ይሁን።
የኢንም መስፈሪያ አራተኛ እጅ በሆነ ተወቅጦ በተጠለለ ዘይት የተለወሰ የኢፍ መስፈሪያ አሥረኛ እጅ መልካም ዱቄት ለእህል ቁርባን ታቀርባለህ።