La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




1 ነገሥት 13:22 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ይህን በማድረግ ፈንታ እኔ በዚያ ምንም ዓይነት እህል ውሃ እንዳትቀምስ ወዳዘዝኩህ ቦታ ተመልሰህ በላህ፤ ይህንንም በማድረግህ ምክንያት ትገደላለህ፤ ሬሳህም በቤተሰብህ መቃብር አይቀበርም።’”

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ተመልሰህ በመምጣት እንዳትበላና እንዳትጠጣ በነገረህ ቦታ እንጀራ በላህ፤ ውሃም ጠጣህ። ስለዚህ ሬሳህ በአባቶችህ መቃብር አይቀበርም’ ” ሲል ጮኾ ተናገረው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ይህን በማድረግ ፈንታ እኔ በዚያ ምንም ዐይነት እህል ውሃ እንዳትቀምስ ወዳዘዝኩህ ቦታ ተመልሰህ በላህ፤ ይህንንም በማድረግህ ምክንያት ትገደላለህ፤ ሬሳህም በቤተሰብህ መቃብር አይቀበርም።’ ”

Ver Capítulo

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ተመ​ል​ሰ​ህም፦ እን​ጀራ አት​ብላ፥ ውኃም አት​ጠጣ ባለህ ስፍራ እን​ጀራ በል​ተ​ሃ​ልና፥ ውኃም ጠጥ​ተ​ሃ​ልና ሬሳህ ወደ አባ​ቶ​ችህ መቃ​ብር አይ​ገ​ባም።”

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ተመልሰህም እንጀራ አትብላ፤ ውሃም አትጠጣ፤ ባለህ ስፍራ እንጀራ በልተሃልና፤ ውሃም ጠጥተሃልና ሬሳህ ወደ አባቶችህ መቃብር አይደርስም’” ብሎ ጮኸ።

Ver Capítulo



1 ነገሥት 13:22
8 Referencias Cruzadas  

ከይሁዳ ለመጣው ለእግዚአብሔር ሰው እንዲህ አለው፤ “ጌታ እንዲህ ይላል፦ ‘ጌታ አምላክህ ያዘዘህን ትእዛዝ ባለመታዘዝ የጌታን ቃል አላከበርክም።


የእግዚአብሔርም ሰው በልቶና ጠጥቶ ካበቃ በኋላ፥ ያ መልሶ ያመጣዉ ነቢይ አህያውን ጫነለት።


በገዛ ራሱም ቤተሰብ መቃብር ቀበረው፤ እነርሱም “ወንድሜ ሆይ! ወንድሜ ሆይ!” እያሉ አለቀሱለት።


እስራኤላውያንም ሁሉ በማዘን አልቅሰው ይቀብሩታል፤ የእስራኤል አምላክ ጌታ የተደሰተበት ልጅ እርሱ ብቻ ስለ ሆነ ከኢዮርብዓምም ቤተሰብ መካከል ሥርዓተ ቀብር በሚገባ የሚፈጸምለት እርሱ ብቻ ይሆናል።


ከወገኖችና ከነገዶችም ከቋንቋዎችም ከአሕዛብም የሆኑ ሰዎች ሦስት ቀን ተኩል በድናቸውን ይመለከታሉ፤ በድናቸውም ወደ መቃብር እንዲገባ አይፈቅዱም።