La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ዘፍጥረት 24:18 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እርሷም፦ “ጌታዬ ሆይ፥ ጠጣ” አለችው፥ ፈጥናም እንስራዋን በእጇ አውርዳ አጠጣችው።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

እርሷም፣ “ጌታዬ፤ ጠጣ” አለችው፤ ፈጥናም እንስራዋን ወደ እጇ አውርዳ አጠጣችው።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

እርስዋም “እሺ ጌታዬ ጠጣ” አለችና እንስራዋን ከትከሻዋ አውርዳ ዘንበል አድርጋ ያዘችለት።

Ver Capítulo

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

እር​ስ​ዋም፥ “ጌታዬ ሆይ፥ ጠጣ” አለ​ችው፤ ፈጥ​ናም እን​ስ​ራ​ዋን ከጫ​ን​ቃዋ በእ​ጅዋ አው​ርዳ እስ​ኪ​ረካ አጠ​ጣ​ችው።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

እርስዋም፦ ጌታዬ ሆይ ጠጣ አለችው ፈጥና፥ እንስራዋን በእጅዋ አውርዳ አጠጣችው።

Ver Capítulo



ዘፍጥረት 24:18
6 Referencias Cruzadas  

ውኃ እጠጣ ዘንድ እንስራሽን አዘንብዪ የምላት እርሷም አንተ ጠጣ፥ ግመሎችህን ደግሞ አጠጣለሁ የምትለኝ ቆንጆ፥ እርሷ ለባርያህ ለይስሐቅ ያዘጋጀሃት ትሁን፥ በዚህም ለጌታዬ ምሕረትን እንዳደረግህ አውቃለሁ።”


ፈጥናም እንስራዋን ከጫንቃዋ አወረደችና፦ ‘አንተ ጠጣ፥ ግመሎችህንም ደግሞ አጠጣለሁ’ አለች፥ እኔም ጠጣሁ፥ ግመሎቼንም ደግሞ አጠጣች።


ውሃም ልታመጣለት በመሄድ ላይ ሳለች ወዲያውኑ ጠርቶ “እባክሽ በተጨማሪ ትንሽ እንጀራ አምጪልኝ” አላት።


በጥበብ ትናገራለች፥ የርኅራኄም ሕግ በምላስዋ አለ።


በመጨረሻም ሁላችሁ በአንድ ልብ ሁኑ፤ እርስ በእርሳችሁ ተሳሰቡ፤ በወንድማማችነት ፍቅር ተዋደዱ፤ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ።