መክብብ 6:4 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በከንቱ መጥቷል በጨለማ ይሄዳል ስሙም በጨለማ ይሸፈናል፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም ምክንያቱም በከንቱ ይመጣል፤ በጨለማም ይሄዳል፤ ስሙም በጨለማ ተሸፍኗል። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ያ ጭንጋፍ ተረስቶ ወደሚቀርበት ጨለማ ስለሚወሰድ ቀድሞውኑ ሳይወለድ ቢቀር በተሻለው ነበር። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በከንቱ መጥቶአል፥ በጨለማም ይሄዳል፥ ስሙ በጨለማ ይሸፈናልና። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በከንቱ መጥቶአል በጨለማ ይሄዳል ስሙም በጨለማ ይሸፈናል፥ |
ሰው መቶ ልጆች ቢወልድ፥ እጅግ ዘመንም በሕይወት ቢኖር፥ ዕድሜውም እጅግ ዓመት ቢሆን፥ ነገር ግን ነፍሱ መልካምን ነገር ባትጠግብ፥ መቃብርንም ባያገኝ፥ ከእርሱ ይልቅ ጭንጋፍ ይሻላል አልሁ።