ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ መጽሐፈ ጥበብ 19:3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)3 ገና በልቅሶ ሳሉ፥ በመቃብሮቻቸውም ላይ ሲጮኹ ልዩ የስንፍና ዐሳብ ስቧቸዋልና፥ ከእነርሱ ይሄዱ ዘንድ ማልደው ያስወጧቸውን እንደ ኰበለሉ ሰዎች ይከተሏቸው ዘንድ በሩጫ ገሠገሡ። ምዕራፉን ተመልከትመጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)3 በኀዘን ላይ ሳሉ፥ በሞቱባቸው ዘመዶቻቸው መቃብር ላይ በመሪር ኀዘን ያለቅሱ በነበሩበት ጊዜ፥ ሌላ የእብደት ሐሳብ ብልጭ አለባቸው፤ ያባረሯቸውንና እንዲወጡ የለመኗቸውን ሰዎችም እንደ ኮብላዮች ያሳድዷቸው ጀመር። ምዕራፉን ተመልከት |