መጽሐፈ ጦቢት 11:16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ጦቢት ግን በፊታቸው እግዚአብሔርን አመሰገነ፤ እግዚአብሔር ይቅር ብሎታልና። ጦቢትም ወደ ምራቱ ወደ ሣራ በደረሰ ጊዜ፥ “ልጄ! እንኳን በደኅና ገባሽ!” ብሎ መረቃት፤ ወደ እኛ ያመጣሽ እግዚአብሔርም ይመስገን፤ አባትሽንና እናትሽንም ይባርክ” አላት። በነነዌም ለሚኖሩ ለወንድሞቹ ሁሉ ታላቅ ደስታ ሆነ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ጦቢት ደስ ብሎት እግዚአብሔርን እያመሰገነ የልጁን ሚስት ለመቀበል ወደ ነነዌ በር ወጣ። የነነዌ ሰዎች ጦቢትን ማንም ሳይመራው ሲራመድና ሲዘዋዋር ባዩት ጊዜ ተደነቁ። |